የኦሮሞ ነጻነት ግንባር በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሸዋ ዞን ዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም የተፈጸመ ግድያ “በገለልተኛ አካል እንዲጣራ” ጥሪ አቀረበ።
ኤኮዋስ በኒጀር ላይ ከተጣሉ ማዕቀቦች የተወሰኑትን አነሳ። የደቡብ አፍሪካው ገዢ ፓርቲ የአፍሪካ ብሔራዊ ኮንግረስ ደጋፊዎች የጫነ ተሽከርካሪ ዛሬ ጠዋት በገጠመው አደጋ ዘጠኝ ሰዎች ሞቱ። የቀድሞው የናሚቢያ ፕሬዝደንት ሐጌ ጋይንጎብ ሥርዓተ-ቀብር ዛሬ እሁድ ተፈጸመ። በፓሪስ የተካሔደ ውይይት ሐማስ ታጋቾችን እንዲለቅ እና በጋዛ ተኩስ እንዲቆም ሊያደርግ ወደሚችል ሥምምነት ሊያመራ እንደሚችል “መግባባት” መኖሩን አሜሪካ አስታወቀች።