አንጋፋ ባልደረቦቻችን መሸኘት ደጋግሞናል፤ የረዥም ዓመታት ባልደረባችን፤ በኢየሩሳሌም የዶቼ ቬለ ዘጋቢ የነበረው አንጋፋው ጋዜጠኛ እና ደራሲ ዜናነህ መኮንን ከዚህ ዓለም ድካም አርፏል። በዕለቱ የዜና መጽሔት ከምንዳስሳቸው ጉዳዮች አንዱ ነው፤
ትግራይ ክልል የፖለቲካ ልሂቃን ውዝግብንም የሚያስቃኝ ዘገባ አለን፤ ተመራጩ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ከወዲሁ ካቢኔያቸውን በማዋቀር እንዲሁም ወደተለያዩ ሃገራት መሪዎች ስልክ በመደወል ተጠምደዋል። የዜና መጽሔት ይህንንም ይዳስሳል።