Sign up to save your podcastsEmail addressPasswordRegisterOrContinue with GoogleAlready have an account? Log in here.
''Continental Drift' is a program tracking the tectonic changes reshaping Africa and redefining the Global South's role in the world. The show explores how policies, markets, and innovation intersect ... more
FAQs about Continental Drift:How many episodes does Continental Drift have?The podcast currently has 8 episodes available.
January 02, 2026ኃይል፣ ወደብ እና ቅርስ፡- የኢትዮጵያ የወደፊት ዕጣ እና የሉዓላዊነት ትግልየአፍሪካ ቀንድ እና የቀይ ባህር ቀጠና በጂኦፖለቲካዊ ውጥረት ውስጥ ናቸው። እስራኤል ለሶማሌላንድ የሰጠችው ዕውቅና፣ የሁቲ አማጽያን ዛቻ እና ከእስራኤል ጋር የገብበት ፍጥጫ ቀጥሏል፡፡ በሌላ በኩል፣ ከመቅደላ የተዘረፉ ቅርሶቻችንን ከብሪታኒያ ሙዚየም "በብድር" ሳይሆን በክብር የመመለስ ትግል የአፍሪካዊያን ሌላ ሜዳ ሆኗል።"እስራኤል ለሶማሌላንድ ስትራቴጂካዊ ቦታ እና አስፈላጊነት ትኩረት እየሰጠች ነው፤ ምክንያቱም ሁቲዎች በእስራኤል ወታደራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ኢላማዎች ላይ ተደጋጋሚ ጥቃት እየሰነዘሩ ነው። ስለዚህ ይህ አንዱ ጉዳይ ነው።" ሲሉ የፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ምሁሩ ዳዊት መዝገበ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ በዛሬው የኮንቲነንታል ድሪፍት መሰናዶ የሶማሌላንድ የሀገርነት እውቅናና ትርጓሜውን ከፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ምሁሩ ዳዊት መዝገበ ጋር እንፈትሻለን። ተዘርፈው ለእይታ የሚቀርቡበት የብሪታኒያ ሙዚየም ቅርሶችን "በውሰት" ለአፍሪካ ሀገራት የመስጠት እቅድና የተዘረፉ ቅርሶችን የማስመለስ ሂደት የትግል መልክን በተመለከተም ከቅርስ አስተዳደር እና ጥበቃ ከፍተኛ ተመራማሪ ተስፋዬ አራጌ ጋር እንወያያለን።ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ ፡...more1h 0minPlay
December 30, 2025የአፍሪካ የሉዓላዊነት ትግል፡ በባለብዙ-ዋልታ ዓለም ውስጥ የአስተሳሰብ ነጻነትአፍሪካ በአሁኑ ወቅት የዓለም የኃይል ሚዛን በሚቀያየርበት ባለብዙ-ዋልታ ዓለም ውስጥ የራሷን ድምፅ ለማሰማት እና የፖለቲካ ተጽዕኖዋን ለማሳደግ እየጣረች ትገኛለች።"እንደሚታየው አፍሪካ እና እስያ በተለይም ከሩሲያ ጋር ያላቸው ግንኙነት ዘርፈ ብዙ ነው። በትምህርት ረገድም ሰፊ ግንኙነት አለን። እንደ አጋጣሚ ሆኖ አፍሪካ ውስጥ ከሩሲያ ትምህርትን እና ሌሎች ድጋፎችን ለማግኘት የሚያስችሉ የዳታ ማኔጅመንት ዕቅዶች አሉን።" ሲሉ በወሎ ዩኒቨርሲቲ የዓለም አቀፍ ግንኙነት እና የፖለቲካ ኢኮኖሚ መምህር ይመር አሊ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።በዛሬው የኮንቲነንታል ድሪፍት ዝግጅታችን፣ አፍሪካ በባለብዙ-ዋልታ ዓለም ውስጥ ያላትን ስልታዊ ቦታ እና ከሩሲያ ጋር ያላትን ተግባራዊ ግንኙነት በወሎ ዩኒቨርሲቲ የዓለም አቀፍ ግንኙነት እና የፖለቲካ ኢኮኖሚ መምህር ከሆኑት ይመር አሊ ጋር እንፈትሻለን። በመቀጠልም፣ የአስተሳሰብ ሉዓላዊነትን እና አፍሪካዊ የሆኑ የንድፈ-ሀሳብ እውቀቶችን የማዳበር አስፈላጊነትን የ"ካፒታል ቫዮለንስ " መጽሐፍ ጸሐፊ ዋቪንያ ማካይ ጋር በጥልቀት እንወያያለን።ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ፡...more1h 0minPlay
December 18, 2025የኢትዮጵያ የቅመማ ቅመም ምርት አዲስ መልክየኢትዮጵያ የቅመማ ቅመም ዘርፍ ባለው ከፍተኛ እምቅ አቅም ልክ ተገቢውን ዋጋ አላገኘም። በሌላ በኩል ደግሞ አፍሪካ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማስፈን በደቡብ-ደቡብ ትብብር እና በሩሲያ-አፍሪካ ትብብር ላይ እየሰራች ነው።የጓሮ እርሻዎች ተባባሪ መስራችና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ቅድስት አምዴ "እኛ ጋር ወደ 23 የሚደርሱ የምግብ ቅመሞች አሉ። ከእነዚህ ውስጥ አንዳንዶቹን እናውቃቸዋለን፤ አንዳንዶቹን አናውቃቸውም። ወደ 800 የሚጠጉ የመድኃኒት ዕፅዋትም አሉን። ይህ በጣም ሰፊ የልዩ ልዩ ዝርያዎች ሀብት ነው። በየቦታው አይገኝም። ስለዚህ በኢትዮጵያ ውስጥ ትልቅ ዕድል አለ ብዬ አስባለሁ።" ስትል ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግራለች፡፡ በዛሬው የኮንቲነንታል ድሪፍት ዝግጅታችን፣ የጉዋሮ ማይክሮ-ፋብሪካዎች የአርሶ አደሩን ገቢ እና የሀገርን የግብርና ዘርፍ መዋቅር እንዴት እየቀየሩ ነው? የሚለውን እንመለከታለን። ለዚህም የጓሮ እርሻዎች ተባባሪ መስራች እና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ቅደስት አምዴን ጋብዘናል። እንዲሁም፣ የሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ የግብርና ኮሌጅ ዲን ዘሪሁን ደምረው (ዶ/ር) እና ሌሎች ዓለም አቀፍ ባለሙያዎች አፍሪካ የምግብ ሉዓላዊነትን በቴክኖሎጂ፣ በፋይናንስና በትብብር እንዴት ታረጋግጣለች? በሚለው ዙሪያ ያደረጉትን ውይይት እንፈትሻለን። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ ፡...more1h 0minPlay
December 15, 2025ኃይል፣ ትብብር እና ምርት፡ የአፍሪካ አዲሱ የሉዓላዊነት መንገድ"[...] የብሪክስ ቁልፍ መርህ የሉዓላዊነትን ማስከበር፣ የሀገራዊ ሁኔታዎችን እና ነባራዊ እውነታዎችን ማክበር ነው። በኢነርጂ ዘርፉም ቢሆን የምናደርገው ትብብር ይህንን ያገናዘበ ነው።" ሲሉ የሩሲያ የኢነርጂ ኤጀንሲ ተወካይ አናስታሲያ ሺሮኮግራድ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። በዛሬው የኮንቲነንታል ድሪፍት ዝግጅታችን፣ ሶስት የተለያዩ ወሳኝ ጉዳዮችን እንመለከታለን በቀዳሚነ የብሪክስ የኢነርጂ ትብብር ለኢትዮጵያ ምን ይዞ መጥቷል ፣ ለአፍሪካ የኢነርጂ ሉዓላዊነትስ ምን ማለት ነው ስንል የሩሲያ ኢነርጂ ኤጀንሲ ተወካይ አናስታሲያ ሺሮኮግራድ አነጋግረናቸዋል፡፡ በሁለተኛው ክፍል ከታህሳስ 2 እስከ 3 በአዲስ አበባ የተካሄደውን የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት ኮንፍረንስ መነሻ አድርገን አፍሪካንና የሃይል ትስስርን እንዲሁም የብሪክስ ጥምረትን ሚና ከኬንያ ኢነርጂ ሚኒስቴር የታዳሽ ኃይል ረዳት ዳይሬክተር ጆርጅ ኒዮንጋዮ፣ ከአፍሪካ ልማት ባንክ የኢነርጂ ብቃት ባለሙያ ጃሌል ቻብቹብ እና ከሌሎች የጉባዔው ተሳታፊዎች ሀሳባቸውን ጠይቀናል። የሀገር ውስጥ አምራቾች የገበያውን ክፍተት እንዴት እየሸፈኑ ነው? የ ቅመም ዕፅዋት ውጤቶች መስራች መቅደላዊት ያሬድ እና ዲዛይነት ቤተልሄም ጌታቸው ያነጋገንበት ጉዳይም በዚሁ መሰናዶ ውስጥ ተካትቷል።ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ ፡...more1h 0minPlay
November 19, 2025ከፖሊሲ አውጪነት ወደ ፖሊሲ ተቀባይነት :- በዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይ.ኤም.ኤፍ) የተደቀኑ ፈተናዎች በአፍሪካአፍሪካ በአንድ ዓመት ውስጥ ከ70 ቢሊዮን ዶላር በላይ ለእዳ ክፍያ በማውጣት፣ ከጤናና ትምህርት በለጠ የፋይናንስ ጫና ውስጥ ወድቃለች ። " አለምዓቀፉን የገንዘብ ተቋም በተቀበልክ ጊዜ፣ የማክሮ ፖሊሲህን በሙሉ አሳልፈህ ትሰጣለህ። እኔ የማክሮ ኢኮኖሚክስ ፕሮፌሰር ነኝ፤ ሁሉንም ፖሊሲዎች አውቃለሁ። ከአይ.ኤም.ኤፍ. ጋር ስምምነት ስትፈጽም፣ የማክሮ ፖሊሲ የመወሰን አቅምህን በጠቅላላ ታጣለህ። የፊስካል ፖሊሲ ታጣለህ፤ የገንዘብ ፖሊሲ ታጣለህ፤ የኢኮኖሚ ፖሊሲ ታጣለህ። በመሠረቱ ራስን በራስ የማስተዳደር አቅምህን ታጣለህ።" ሲሉ የማክሮ ኢኮኖሚክስ እና ኢንተርናሽናል ኢኮኖሚክስ ፕሮፌሰር አለማየሁ ገዳ (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። በዛሬው የኮንቲነንታል ድሪፍት ዝግጅታችን፣ የአፍሪካን ዕጣ ፈንታ የሚወስነው ማን ነው? በሚለው ሀሳብ ዙሪያ የማክሮ ኢኮኖሚክስ እና ኢንተርናሽናል ኢኮኖሚክስ ፕሮፌሰር አለማየሁ ገዳ (ዶ/ር) ሰፊ ውይይት አድርገናል፡፡ የኢትዮጵያ የወይን ዘርፍ በአለምአቀፍ ገበያ እንዴት ተወዳዳሪ መሆን ይችላል ? የብሪክስና የደቡብ ለደቡብ ትብብሮችስ ምን አይነት እድልና አቅሞች ይፈጥሩለታል ስንል ከወይን ባለሙያ ዳዊት ዳንኤል ጋር ሰፊ ውይይትን አድርገናል።ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ ፡...more1h 0minPlay
November 14, 2025ፍትህ በችሎት ላይ : የአፍሪካ ድምፆች ከአለምዓቀፍ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ባሻገርፍትህ የውጭ ተጽዕኖን ሲከናነብ ፣ ማን ይዳኛል ? ማንስ ደግሞ በነጻ ይለቀቃል? '' የዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት (አይሲሲ) ምስረታን ስንመለከት፣ አብዛኞቹ ለክስ የሚቀርቡ ጉዳዮች የአፍሪካ ጉዳዮች ሆነው እናገኛቸዋለን። በአህጉር አቀፍ ደረጃ ለጦርነቶች አስተዋጽኦ የሚያደርጉት አብዛኞቹ ሀገራት ግን የአፍሪካ ሀገራት አይደሉም። ስለዚህ እንደ አፍሪካውያን የዉስጥ ጉዳዮቻችንን የምናይበት የአፍሪካ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት የምናቋቁምበት ጊዜ አሁን እንደሆነ አምናለሁ። ራሳቸውን ከአይሲሲ ቻርተር ያገለሉትን የአፍሪካ ሀገራትንም ማድነቅ ወይም ማመስገን እወዳለሁ '' ስትል የአፍሪካ የህግ ተማሪዎች ፌዴሬሽን ዓለም አቀፍ ዋና ጸሐፊ ግሎሪያ ሲሲያ ምማሲ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግራለች።በዚሁ የኮንቲነንታል ድሪፍት መሰናዶ ሁለት የተለያዩ ግን ወሳኝ ጉዳዮችን እናያለን ፣ አፍሪካዊያን ለምዕራባዊያ ባደሩ የ'ፍትህ ተቋማት ስለሚፈጸምባቸው በደልና እና የአፍሪካ ሀገራት አማራጮች ምንድን ናቸው ስንል የአፍሪካ የህግ ተማሪዎች የቀድሞ ተመራቂዎች ኮሚሽን ፌዴሬሽን ከፍተኛ ኮሚሽነር አልፍሬድ ኤሊ ፣ የአፍሪካ የህግ ተማሪዎች ፌዴሬሽን ዓለም አቀፍ ዋና ጸሐፊ ግሎሪያ ሲሲያ ምማሲን እና የአፍሪካ የህግ ተማሪዎች ፌዴሬሽን የሰሜን አፍሪካ ክልላዊ ዳይሬክተር ራታኒያ ዳዊን ጠይቀናል፡፡ በሌላኛው ጉዳያችን ደግሞ የአፍሪካ የግብርናና ገጠር ልማት ጦችን ለማስመዝገብ አፍሪካ ምን ማድረግ አለባት ስንል የኢንተር አፍሪካ ፊቶሳኒተሪ ካውንስል አስተባባሪ ዶ/ር ሳሊዩ ኒያሲ፣ የአፍሪካ ህብረት የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የሰማያዊ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ አካባቢ ኮሚሽነር ሞሰስ ቫላካቲ እና ሌሎችንም አነጋግረናቸዋል፡፡ ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ ፡...more1h 0minPlay
November 14, 2025የባህላዊ የሙዚቃ መሳሪያዎችና የዉዝዋዜዎች ኃይል - ማንነትን ለመግለጥና ለምጣኔ ኃብታዊ እድገትኢትዮጵያ የብዝሃ ሀብት ባለቤት ናት ፣ ተፈጥሮ ካደላት መገለጫዎቿ እኩሌታ ብዙኃ ቋንቋና ባህል ያላት መሆኑ የልዩ መልካነቷ ማሳያ ነው፡፡ ባህላዊ ውዝዋዜዎችና የሙዚቃ መሳሪያዎቿም ትናንቷን የሚዘክሩ ፣ የነገን መልክ ዛሬ ላይ ለመቅረጽ በብዙ የሚጥሩ ናቸው፡፡ እንዴት ? “ አንደኛ የስራ እድል ምንጭ ይሆናል። የሚጫወቱ ሰዎች ቢበዙ የስራ እድል ነው ብዙ ሙዚቀኛ በዚህ ሙያ ላይ ያሉ ሙዚቀኞች እንደመኖሪያቸው ይሆናል። ሁለተኛ ደግሞ የሀገር ሀብት ነው። እንደ ሀገርም መሸጥ ይቻላል ሙዚቃን መሸጥ ይቻላል ፣ በነገራችን ላይ ያው [ከኢትዮጵያ ኢኮኖሚ አንጻር] በተለያየ መንገድ ገቢ ማግኘት አለብን ብዬ አስባለሁ። እና አንደኛው ሙዚቃ ነው፡፡ ሙዚቃ በትልቁ ገቢ ማምጣት ይችላል ብዬ አስባለሁ ፤ ከሌላው አለም። ሙዚቃችንን ብንሸጠው እንደ ሀገር እንጠቀማለን። ዋናው ደግሞ የኢትዮጵያን ጥሩ ገጽታ ታስተዋውቂበታለሽ። ” ሲል የሙዚቃ አጥኚው እና የሞሰብ ባንድ መስራች ጣሰው ወንድም ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግሯል፡፡ በዛሬው የኮንቲነንታል ድሪፍት ዝግጅታችን የኢትዮጵያዊያንን ማንነት ለመላዉ ዓለም ስለሚያንጸባርቁ ባህላዊ ዉዝዋዜዎች እና በኢትዮጵያዊያን መገለጫ ስለሆነው ዋሽንት አንስተን ስለባህላዊ የሙዚቃ መሳሪያዎችና ሁሉንአቀፍ አቅማቸው በሰፊው እንነጋገራለን ፤ ለዚህም የፈንዲቃ ባህል ማዕከል መስራች መላኩ በላይ እና የሞሰብ ባንድ መስራች ጣሰው ወንድም ጋብዘናቸዋል፡፡ ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ ፡...more1h 0minPlay
October 28, 2025መጭውን ጊዜ መቅረጽ፡ የእንጨት ስራ ዉጤቶችና የፋሽን ዘርፍ ለኢትዮጵያ ፈጠራ ኢኮኖሚኢትዮጵያ በየዓመቱ ከ170 ሚሊዮን ዶላር በላይ ከውጪ ለምታስገባው የእንጨት ዉጤቶች ወጪን ታወጣለች ። [...]መንግሥት የእንጨት ሥራ ውጤቶች ከውጭ እንዳይገቡ ለማድረግ ወይም ቢያንስ ለመቀነስ ዉሳኔ አሳልፏል። ነገር ግን በውስጡ ያሉ የፖሊሲ ጉዳዮች ምክንያት ይህ ውሳኔ ተሰርዟል፣ የእንጨት ውጤቶች እንደገና ለማስገባት ተፈቅዷል። ነገር ግን ክልከላው በተጣለበት አስር ወራት ጊዜ ውስጥ እንኳን በሀገር ውስጥ ገበያው ፍላጎት ምክንያት ብዙ ሀገር በቀል የእንጨት ሥራ ውጤት ላይ የተሰማሩ ኩባንያዎች በየአቅጣጫው መጥተው አይተናቸዋል።” ሲሉ የዋሪት ሙሉጥላ ኢንተርናሽናል ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የኢትዮጵያ ፈርኒቸር አምራቾች ማህበር ፕሬዚዳንት ትህትና ለገሰ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል ። በዛሬው የኮንቲነንታል ድሪፍት ዝግጅታችን የኢትዮጵያ የእንጨት ስራ ዉጤቶችና የፋሽን ዘርፍ ለሀገሪቱ የፈጠራ ኢኮኖሚ ያላቸውን ሚና ፣ ፈተናና እድሎች በሰፊው እንመለከታለን፡፡ ለዚህም የዋሪት ሙሉጥላ ኢንተርናሽናል ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የኢትዮጵያ ፈርኒቸር አምራቾች ማህበር ፕሬዚዳንት ትህትና ለገሰ እና የፓራዳይዝ ፋሽን ባለቤትና ዲዛይነት ገነት ከበደን ጋብዘናቸዋል፡፡ መረጃውን ለማግኘት ሙሉ ፕሮግራሙን ያዳምጡ ፡...more1h 0minPlay
FAQs about Continental Drift:How many episodes does Continental Drift have?The podcast currently has 8 episodes available.