Sign up to save your podcastsEmail addressPasswordRegisterOrContinue with GoogleAlready have an account? Log in here.
የዓለም አቀፍ የኃይል ሚዛን እየተቀየረ ባለበት በዚህ ወቅት - ኢትዮጵያን፣ አፍሪካን እና ሌሎችን የሚቀርጹ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ሃይሎች ወደምንመለከትበት ወደ “ራይዚንግ ሳዉዝ” እንኳን በደህና መጡ፡፡ ደቡባዊ አመለካከቶችን ወደ ዓለም አቀፋዊ ውይይት መድረክ ስናቀርብ የአሰላሳዮችን ፣ የመሪዎችን እና ... more
FAQs about The Rising South:How many episodes does The Rising South have?The podcast currently has 140 episodes available.
August 27, 2025የኢትዮጵያ የመጨረሻውን ንጉሠ ነገሥት የአጼ ኃይለ ሥላሴ 50ኛ ሙት ዓመት ሲታወስ“እንግሊዞች ኢትዮጵያን በፋሺዝም ወረራ ወቅት አገዝን ብለው እንደገና እኮ በእንግሊዝ ስር ለማድረግ ነበረ ትልቁ ጥረታቸው። ከዛ መንጋጋ ውስጥ ነው እኮዛ አውጥተው ነጻ ሀገር የሰጡን፡፡ትልቅ የዲፕሎማሲ ስኬት ነው እሱ ራሱ፡፡” ጋዜጠኛ ጥበቡ በለጠ በዚህኛው የራይዚንግ ሳዉዝ ዝግጅታችን፣ ንጉሠ ነገሥት ግርማዊ ቀዳማዊ አጼ ኃይለ ሥላሴ ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩበትን 50ኛ ዓመት በማስመልከት ዘላቂ የሆነውን የተወሳሰበ ታሪካቸውን እንመረምራለን። በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ቦታ የሚሰጣቸው ንጉስ የነበሩት አጼ ኃይለ ሥላሴ ለአለም አቀፍ አመራራቸው፣ ለዘመናዊነት ያደረጉትን ተጋድሎ እንዲሁም በአፍሪካ አንድነት ውስጥ ላላቸው ተምሳሌታዊ ሚና ይታወሳሉ። በንጉሠ ነገሥቱ የሕይወት ታሪክ ላይ በስፋት የሠሩት ጋዜጠኛ ጥበቡ በለጠ፣ ስለ አጼ ኃይለ ሥላሴ የግል እና የፖለቲካ ጉዞ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተውናል፡፡...more1h 0minPlay
August 25, 2025የኢትዮጵያ የባቡር ትራንስፖርት መነቃቃት እና ለቀጣናዊ ውህደት ያለው ሚና“በጭነት መኪናዎች ከአራት እስከ ሰባት ቀናት ይወስዳል። በኤሌክትሪክ ኃይል በሚሠራ ባቡር ግን ከ12 እስከ 18 ሰዓታት ብቻ ይወስዳል፤ ከአንድ ቀን ያነሰ ጊዜ። የጭነት ወጪዎችን ይቀንሳል፣ ከመኪና ትራንስፖርት ጋር ሲነጻጸር ትልቅ ቅናሽ ያደርጋል።” በዚህ የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት፣ ኢትዮጵያ የባቡር መሠረተ ልማቷን ለማዘመን ያደረገችውን እና በማድረግ ላይ ያለችውን እንቅስቃሴ እንቃኛለን — ይህም የአገሪቱ የኢኮኖሚ ሽግግር እና የቀጣናዊ ትስስር ርዕይ ወሳኝ ምሰሶ ነው። የኢትዮጵያ የባቡር ምህንድስና ማህበር ፕሬዝዳንት ኢንጂነር መኮንን ጌታቸው በዘርፉ የታየውን ለውጥ እና የባቡር ትራንስፖርት ለሀገር ልማት ያለውን ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ በሰፊው ያብራራሉ።...more30minPlay
August 19, 2025የሰላም ተስፋ፦ የአላስካው ስብሰባ አንድምታዎችሳለፍነው ሳምንት በአላስካ የተካሄደው ጉባኤ በታሪክ ተመራማሪዉ ፕሮፌሰር አየለ በክሪ ገለፃ የአውሮፓውያን እና የዩክሬንን እንቅፋቶችን ተሻግሮ የተከናወነ ነው። ውይይቱ ግን ለዓለም አቀፍ ስጋቶችም መፍትሄ የመሆን ተስፋን የሰጠ ነው።በሩሲያ እና በአሜሪካ የሚደረግ ስምምነት ሌሎች ዓለም አቀፍ ስጋቶችን ለመፍታት እንደ ማዕቀፍ ሊያገለግል ይችላል -ፖለቲካ ሳይንስ እና የዓለምአቀፍ ግንኙነቶች ባለሙያ በፍቃዱ ዳባበዚህኛው የራይዚንግ ሳዉዝ ዝግጅታችን የፕሬዝደንት ፑቲን እና የፕሬዝደንት ትራምፕን የአላስካ ስብሰባ በጥልቀት እንዳስሳለን። የመሪዎቹን ዉይይት ቀጣይ ተፅዕኖዎችንም በተመለከተ የታሪክ ምሁርና ተመራማሪዉ ፕሮፌሰር አየለ በክሪ ፣ የሕ/ ተ/ ም/ቤት የውጭ ግንኙነት እና ሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ም/ሰብሳቢ ፈትሂ ማህዲ (ዶ/ር ) ፣ የፖለቲካ ሳይንስ እና የዓለምአቀፍ ግንኙነቶች ባለሙያ በፍቃዱ ዳባን አነጋግሯቸዋል፡፡...more30minPlay
August 12, 2025የአህያ ክሊኒክ፦ በአህዮች እና በባለቤቶቻቸው ህይወት ላይ ያመጣው ለውጥ“የአህዮች ዕድሜ ተሻሽሏል። ቀደም ሲል አንድ አህያ እስከ 10 ዓመት ይኖር ነበር፣ ነገር ግን አሁን እስከ 20 ዓመት ሊኖር ይችላል [...] በተጨማሪም የአህያ ባለቤቶችን በአጠቃላይ [የአህዮች] ደህንነታቸው፣ አመጋገባቸው፣ ማለትም የአመጋገብ ስርዓታቸው፣ የመኖሪያ ቤታቸው ሁኔታ ላይ እናስተምራለን።” ዶ/ር ደረጀ ፀጋዬ፣ የእንስሳት ሐኪምበዚህ የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከአለም አቀፍ አጋሮች ጋር በመተባበር የሚያስተዳድራቸው የእንስሳት ህክምና ክሊኒኮች፣ የአህዮችን ደህንነት በማሻሻል እና በእነሱ ላይ ጥገኛ የሆኑ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ቤተሰቦች እንዴት እንደሚደግፉ እንቃኛለን።የፕሮጀክቱ መሪ አቶ አለማየሁ ፋንታ፣ የእንስሳት ህክምና ባለሙያ ዶ/ር ደረጀ ፀጋዬ እና ከአካባቢው የአህያ ባለቤት አቶ ጥበበ ሰለሞን ጋር ስለ ክሊኒኩ ምስረታ እና ስላመጣው ለውጥ ውይይት አድርገናል፡፡...more30minPlay
August 08, 2025አፍሪካን መመገብ፦ የምግብ ጥገኝነት ሰንሰለትን በመስበር"ቅኝ ገዢዎች ጥለውት የሄዱት ውርሶች አሁንም እንዳሉ አምናለሁ። አሁን ለንግድ እና ለምግብነት የሚውሉ ሰብሎችን ሚዛን ለማስጠበቅ እየሞከርን ነው።" አቡበከር ኪያሪ፣ የናይጄሪያ የግብርና እና ምግብ ዋስትና ሚኒስትር ለዚህ አይነቱ ለውጥ ሀገር በቀል እውቀቶችን መጠቀምም የግድ ይላል።"ወደ ሀገር በቀል እውቀት መመለስ አለብን፣ ምክንያቱም የአየር ንብረት ለውጥን እንድንቋቋም፣ የምግብ ዋስትናን እንድናጠናክር እና ለሚመጣው ትውልድ እውቀትን ለማስተላለፍ የሚረዳ ብዙ እውቀት እየጠፋ ነው።" ዊሊስ ኦቺንግ፣ የኬንያ የገጠር ማጠናከሪያና የግብርና ትራንስፎርሜሽን ለዘላቂነት ማዕከል (ክሪየትስ ኢንተርናሽናል) ዋና ዳይሬክተር ይህ የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት፣ በአዲስ አበባ የተካሄደው የተባበሩት መንግስታት የምግብ ስርዓት ጉባኤ 2025 መነሻዉ አድርጓል። አፍሪካ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የምታደርገውን ጉዞም ይመረምራል። የጉባኤው ተሳታፊ ባለሙያዎችም አህጉሪቱ ከውጭ በሚገቡ ምርቶች ላይ ስላላት ጥገኝነት፣ ራስን ለመቻል እንቅፋት ስለሆኑባት መዋቅራዊ ችግሮች እና ሌሎች ጉዳዮች ላይ ቆይታ አድርገዋል።...more30minPlay
August 06, 2025ሰው ሰራሽ አስተውሎትን ለበጎ መጠቀም፦ ኢትዮጵያዊያን ተማሪዎች የደመቁበት ዓለም አቀፍ ዉድድር“እኛ ምን ያቅተናል?፣ ሀገራችንን ለማሳደግ ምን ያቅተናል?፣ ማይንድሴት /አመለካከት/ ላይ መስራት አለብን ፤ የሁሉም ማይንድሴት ላይ መሰራት አለበት ምክንያቱም [ከሌሎች ሃገራት ተወዳዳሪዎች ጋር] አቅማችን አንድ እንደሆነ አይቻለው፡፡” ተማሪ አቤል ደረጀ በዚህ የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት፣ በጄኔቫ በተካሄደው ዓለም አቀፍ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ውድድር ኢትዮጵያን በኩራት ወክለው 5ኛ ደረጃን ከያዙ ከተማሪ አቤል ደረጄ እና ፍሬወይኒ በላይነህ እንዲሁም ከውድድሩ የኢትዮጵያ ተወካይና አስተባባሪ መንግስቱ ወዳጄ ጋር ቆይታ እናደርጋለን፡፡ በወጣቶች ዘንድ ሰው ሰራሽ አስተዉሎትን ለበጎ የመጠቀም ውድድር አጠቃላይ ሂደቱን፣ የጄኔቫ ቆይታቸው እና ስላገኙት ተሞክሮም ውይይት አድርገናል፡፡...more1h 0minPlay
August 04, 2025ኢትዮጵያ፡ በአገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴ ሰላምን የመገንባት ሂደት“መንግስት ቅጣትና ሪዋርድ [ማበረታቻ] ያመጣብኛል ብሎ ከሚያስበው ነገር ይልቅ ኃጢያትና ጥሩ ነው ተብለው በማህበረሰቡ የተፈረጁን ነገሮች የመቀበል አዝማሚያ አለ አንዳንድ ቦታ ላይ፤ ስለዚህ ማህበረሰባችን ለእነዛ ነገሮች ዋጋ ስለሚሰጥ ሁለቱን የግጭት አፈታት መንገድ (ዘመናዊውንም ባህላዊውንም) አቀናጅተን ችግሮች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ እያደረግን ነው፡፡” አቶ ቸሩጌታ ገነነ፣ በሰላም ሚኒስቴር የፌደራሊም እና ግጭት አስተዳደር ሚኒስትር ዳኤታበዚህ የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት፣ ከአቶ ቸሩጌታ ገነነ ጋር ኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምን ለመገንባት ያላትን የበለጸገ የባህል ቅርስ እንዴት እየተጠቀመች እንደሆነ እንቃኛለን። በዘመናዊ ተግዳሮቶች እና በተለያዩ የባህል መልክዓ ምድሮች መካከል፣ መንግስት በማህበረሰብ ላይ ያተኮረ እርቅ ላይ ያለውን አዲስ ትኩረት፣ እና የአገራዊ ፍትህ ስርዓቶችን ህጋዊ እውቅና መስጠት ላይ ውይይት አድርገናል፡፡...more30minPlay
July 31, 2025ማን ዋጋውን ይከፍላል? የአካባቢ ኢፍትሃዊነት እና በደቡባዊ አለም ላይ የሚሰነዘር ወቀሳ“ምዕራቡ ዓለም በኢንዱስትሪ ልማት ወቅት ማንኛውንም ዋጋ ቢያስከፍል፣ የአካባቢ ተጽእኖዎችን ችላ በማለት የኢኮኖሚ ዕድገትን ተከትሏል። የዛሬው የአካባቢ ቀውስ በአብዛኛው የዚያ አካሄድ ውጤት ነው፣ የተፈጥሮ ሀብቶች ላይ ከፍተኛ ጉዳትን በማድረስ—ምዕራቡ ዓለም ለአለም አቀፍ የአካባቢ ጉዳት ረገድ ታሪካዊ ተጠያቂ ያደርገዋል።” አቶ መልካሙ ኦጎ፣ የአካባቢ ጥበቃ ጠበቃበዚህኛው የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅታችን የአካባቢ ጥበቃ ጠበቃ ከሆኑት ከአቶ መልካሙ ኦጎ ጋር ደቡባዊ አለም ላይ እየደረሰ ስላለው የአካባቢ ኢፍትሃዊነት እና ወቀሳ እንዲሁም ይህን መከላከል ስለሚቻልባቸው መንገዶች ሰፊ ውይይት አድርገናል፡፡...more1h 0minPlay
July 29, 2025የምግብ ቅኝ ግዛት እና የአፍሪካ የምግብ ሉዓላዊነት ፍልሚያ"የውጭ ኩባንያዎች እና የውጭ መንግስታት በዘረመል የተሻሻሉ ሰብሎችን በዋናነት ይቆጣጠራሉ። በእነሱ ቁጥጥር ስር ናቸው። ምናልባት በነጻ ይሰጡናል ማለት ትችል ይሆናል። አንዴ መጠቀም ከጀመርክ በኋላ ግን፣ በብዙ ሌሎች ሀገራት ዘንድ እንዳየነው፣ የእነዚህ ሰብሎች ምርታማነት ይቀንሳል፣ በአካባቢያዊ ስነ-ምህዳር፣ በነፍሳት፣ እንስሳት እና በሌሎችም ይጠቃሉ። [...] የእጅ አዙር ቅኝ ገዢዎች በአፍሪካ ድህነትን አልቀነሱም፣ የተመጣጠነ ምግብ እጥረትን አላጠፉም፣ የገበሬዎችንም ገቢ አልጨመሩም። ያደረጉት ነገር በአፍሪካ ውስጥ ያሉ ወሳኝ፣ ወሳኝ ምግቦችን መተካት ወይም መቀነስ ነው።”በዚህ የራይዚንግ ሳውዝ መሰናዶ በአፍሪካ የምግብ ሉዓላዊነት ህብረት /AFSA/ ዋና አስተባባሪ ሚሊዮን በላይ (ዶ/ር) ጋብዘናቸዋል ፤ ዉይይትም እናደርጋለን።የሚመረቱ፣ የሚበስሉ እና ከምንመገበውም ምግብ ጀርባ ያለ ድብቅ ፖለቲካም እንፈትሻለን።...more1h 0minPlay
July 25, 2025ኢትዮጵያ በአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ስምምነት ትግበራ“አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነቱ ትልቅ ዕድል አለው። በ2045 የአፍሪካን ንግድ በ45 በመቶ ገደማ ማለትም በ275.7 ቢሊዮን ዶላር ይጨምራል […] እንዲሁም የአፍሪካ አገሮች የግብርና ምርቶችን ወደ ውጭ የኢንዱስትሪ ምርቶች እንዲልኩ ይረዳቸዋል።”በዚህ የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት በኢትዮጵያ ፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ተመራማሪ ከሆኑት አበበ አምባቸዉ (ዶ/ር) ጋር በመሆን የታሪፍ ቅነሳን በማስወገድ እና የኢንዱስትሪ እድገትን በማበረታታት የአህጉሪቱን የንግድና ኢኮኖሚያዊ ውህደትን ስለሚያሳድገው የዓለም ትልቁ የነፃ ንግድ ቀጠና ስምምነት ላይ ተወያይተናል ፤ የኢትዮጵያን የመጨረሻ ምዕራፍ ዝግጅቶችንም ዳስሰል።...more30minPlay
FAQs about The Rising South:How many episodes does The Rising South have?The podcast currently has 140 episodes available.