የግንቦት 7 ቀን 2016 ዓ.ም. ዋና ዋና ዜናዎች
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሶዶ ዙሪያ ወረዳ የመንግሥት ሠራተኞች ደሞዝ እንዲከፈላቸው በአደባባይ ሠልፍ ጠየቁ። ሠራተኞቹ ለሁለት እና ለሦስት ወራት ያህል ደሞዝ ባለማግኘታቸው ከነቤተሰባቸው ለችግር መጋለጣቸውን ተናግረዋል።
ደቡብ ሱዳን ዉስጥ ከሰባት ሚሊዮን የሚበልጥ ሕዝብ ለአስከፊ ረሐብ መጋለጡን የተመድ አስታወቀ።
ማዕከላዊ ኬንያ ውስጥ የወረደውን ከባድ ዝናብ ተከትሎ በደረሰው የመሬት መንሸራተት እስካሁን አምስት ሰዎች የገቡበት አልታወቀም።
የስሎቬኪያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሮበርት ፊኮ በዛሬው ዕለት በጥይት ተመትተው ሆስፒታል ገቡ። የተኮሰባቸው ተጠርጣሪ በፖሊስ ተይዟል።