የመጋቢት 3 ቀን 2016 ዓ.ም. ዋና ዋና ዜናዎች
ዩናይትድ ስቴትስ አሸባብን በገንዘብ ይደግፋሉ ባለቻቸው 16 ግለሰቦች እና የንግድ ተቋማት ላይ ማዕቀብ ጣለች።
የሱዳን ጦር የሀገሪቱን ብሔራዊ የራዲዮ እና ቴሌቪዝን ጣቢያ ዋና መሥሪያ ቤት በዛሬው ዕለት በቁጥጥር ሥር ማድረጉን አስታወቀ።
በቀውስ የምትታመሰው የሄይቲ ጠቅላይ ሚኒስትር ከሥልጣን ለመውረድ መስማማታቸውን አስታወቁ።
15 ሰዎችን ያሳፈረ የሩሲያ ወታደራዊ መጓጓዣ አውሮፕላን ከተነሳበት ብዙም ሳይርቅ ተከሰከሰ። ከተሳፋሪዎቹ የተረፈ ሰው ስለመኖሩ የተነገረ ነገር የለም።