"የምዕራቡ ዓለም የዓለም አቀፉን የወንጀል ፍርድ ቤት (አይ.ሲ.ሲ) የራሱን ፍላጎት ማስፈፀሚያ ያደረገው ይመስላል [...] ቻድ ከ አይ.ሲ.ሲ ለመውጣት ያሳለፈችው ውሳኔም ለቀሪው የአፍሪካ አህጉር ግልጽ መልዕክት አስተላልፏል 'አፍሪካ የራሷን ዕድል በራሷ የመወሰን እና የራሷን የፍትህ መንገድ የመቀየስ ጊዜዋ አሁን ነው' የሚል" ሲሉ የሕግ ባለሞያው መታገስ ዉለታው ለስፑትክ አፍሪካ ተናግረዋል።
በዛሬው የድረም ኦቭ ቼንጅስ ቀዳሚ ዝግጅታችን ቻድ ከዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት (አይ.ሲ.ሲ) ለመውጣት የወሰደችውን ርምጃ መነሻ አድርገን የተቋሙን መዋቅራዊ አድልዎ እና በአፍሪካ የሀገርበቀል የፍትህ ስርዓቶችን የመገንባት ጥረቶችን በጥልቀት እንፈትሻለን። ለዚህም በወራቤ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ትምህርት ቤት መምህር እና የዓለም አቀፍ ሕግ ባለሞያ መታገስ ዉለታው ጋር ተወያይተናል።
በሁለተኛው ጉዳያችን ደግሞ፣ እ.ኤ.አ ከሐምሌ 29 እስከ 30፣ 2026 በአዲስ አበባ የተካሄደውን ወርልድ ፐብሊክ ፎረም መነሻ አድርገን፤ የግብርና ዘርፉን ወደ 21ኛው ክፍለ ዘመን በማሸጋገር ረገድ የዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን ሚና እንቃለን። ይህንን ጉዳይ የበለጠ እንዲያብራሩልን ከሩሲያው "ግራሚዮን ፕላስ" ኩባንያ ተወካይ ፓቬል ኮኖቭ ኒኪታ ጋር ተወያይተናል።
ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ: