Sign up to save your podcastsEmail addressPasswordRegisterOrContinue with GoogleAlready have an account? Log in here.
በሣምንቱ በተከሰቱ በዋናነት የኢትዮጵያ እንደ አስፈላጊነቱ የዓለም ዐበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ እና ማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ ዶይቼ ቬለ ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታቸውን በመጋበዝ ውይይት ይካሔዳል። በውይይቱ የመንግሥት ባለሥልጣናት፣ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች፣ በተለያዩ ዘርፎች የተሰማሩ ባለሙያዎች ይጋበዛሉ። በየሣምንቱ እ... more
May 18, 2025የኢትዮጵያ የፓርቲ ፖለቲካ ከ1997 ምርጫ ወዲህ ከወዴት አለ?በ1997 ምርጫ ኢሕአዴግን የተገዳደሩት ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ባለፉት 20 ዓመታት ተዳክመዋል። ኢሕአዴግን በብልጽግና ፓርቲ የተካው ለውጥ ያነቃቃቸውም በውስጣቸው ተከፋፍለዋል። የፓርቲ ፖለቲካ በኢትዮጵያ ሞተ ወይስ እያጣጣረ ነው? ዶክተር ብዙነህ ጌታቸው እና ዶክተር አዲሱ ላሽተው የተሳተፉበት የእንወያይ መሰናዶ የኢትዮጵያን የፓርቲ ፖለቲካ ህልውና ከ1997 ወዲህ እና በሚቀጥለው ዓመት ሊካሔድ ከታቀደው ምርጫ አኳያ ይዳስሳል።...more44minPlay
March 16, 2025የኢትዮጵያ ባንኮች ውህደት፦ በግዳጅ ወይስ በገበያው ፍላጎት?የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ያዘጋጀው ረቂቅ መመሪያ ሲጸድቅ አንድ ባንክ በልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች ቅርንጫፍ ከፍቶ ለመሥራት የሚያስችለውን ፈቃድ ለማግኘት 66 ቢሊዮን ብር ገደማ አጠቃላይ ሐብት ሊኖረው ይገባል። ረቂቅ መመሪያ ውህደትን የሚገፋፋ እንደሆነ በባለሙያዎች ዘንድ ግንዛቤ አለ። ይህ ውይይት የባንኮች ውህደትን ፋይዳ እና ተግዳሮት ይፈትሻል። በውይይቱ ከፍተኛ የባንክ ባለሙያ ሆነው በመሥራት ላይ የሚገኙት አቶ ባህሩ ያሲን፣ ለረዥም ዓመታት በከፍተኛ የባንክ ባለሙያነት ያገለገሉት የኢትዮጵያ የሎጂስቲክስ ትራንስፎርሜሽን ቢሮ ዳይሬክተር አቶ ወርቁ ለማ እና የገንዘብ አስተዳደር ባለሙያው ዶክተር አብዱልመናን መሐመድ ተሳትፈዋል።...more47minPlay