“የእነዚህ ተቋማት (አይ.ኤም.ኤፍ እና የዓለም ባንክ ) መሠረታዊ ዳራ፣ ምን እንዲሠሩ ታስበው እንደነበር ወይም ምን እንዲያሳኩ ይጠበቅባቸው እንደነበረ በመነሳት ነው። እኔ እንደ አፍሮ-ሴንትሪስት (አፍሪካን ማዕከል እንደሚያደርግ ሰው)፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት የምዕራባውያንን የበላይነት ከሚያስፋፉ ወኪሎች ጋር ተመሳሳይ ናቸው የሚል ፍጹም የተለየ መከራከሪያ አለኝ። እነዚህ ተቋማት የተቋቋሙት ለአፍሪካ መልካም ጥቅም ነው የሚለውን መመሪያ በመቀበል፣ የምዕራባውያንን ብልሹነት ለማረጋገጥ በምናደርገው ጥረት በበላይነት ፖለቲካቸው ውስጥ ራሳችንን የምናስር ከሆነ፣ መዘንጋት የሌለብን ነገር ይሄ እርዳታ እንዳልነበረ ነው። ይህ በፋይናንስ በኩል የወረራ ተልእኳቸውን የበለጠ ለማስፋፋት የተደረገ ጥረት ነበር።” ሲሉ የ'ዲቨሎፒንግ አፍሪካ ? ኒው ሆራይዘን ዊዝ አፍሮሴንትሪክ' (Developing Africa? New Horizons with Afrocentricity) መጽሐፍ ደራሲ ሌሃሳ ሞሎይ (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡
በዚህ የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት የ ''Developing Africa? New Horizons with Afrocentricity'' መጽሐፍ ደራሲ ሌሃሳ ሞሎይ (ዶ/ር) ጋር ስለ አፍሪካ ዕዳ፣ እርዳታና ስለ ልማት የሚነገሩትን የተለመዱ ትርክቶች እንፈተሻለን።