Sign up to save your podcastsEmail addressPasswordRegisterOrContinue with GoogleAlready have an account? Log in here.
FAQs about DW | Amharic - News:How many episodes does DW | Amharic - News have?The podcast currently has 2,914 episodes available.
April 24, 2025የጤና ባለሙያዎች የደመወዝና የጥቅማ ጥቅም ጥያቄየጤና ባለሙያዎቹ 12 ጥያቄዎችን ለጤና ሚኒስቴር ማቅረባችውን አመልክተው፣ ጥያቄያቻቸው እስከ ግንቦት 3/2017 ዓ ም ምላሸ ካላገኘ የሥራ ማቆም አድማን ጨምሮ ሌሎቸ ህጋዊ ያሉትን እርምጃ እንደሚወስዱ ባለሙያዎቹ አስጠንቅቀዋል፡፡...more5minPlay
April 23, 2025የኢትዮጵያ ፖሊስ የአዲስ ስታንዳድርን መረጃ ወይም ዳታ «እወስዳለሁ» አለየኢትዮጵያ የፌደራል ፖሊስ ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ የአዲስ ስታንዳደርድ ቢሮን መመዝበሩ አልበቃ ብሎ በወሰዳቸዉ ኮምፒዉተሮችና ሞባይሎች ዉስጥ የሚገኙ መረጃዎችን ለመዉሰድ መዛቱን ዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት (CPJ) አጥብቆ ተቃዉሞታል...more3minPlay
April 21, 2025ማሕደረ ዜና፣የሱዳን ዉድመትና የመከፋፈሏ ሥጋትያለመግባባቱ ምክንያቶች ከሩቅ ያሉት በቅኝ ገዢነት ብዙ ጊዜ የሚወቀሱት አዉሮጶች፣ በአረብ ጠላትነት የምትወገዘዉ እስራኤል ወይም አሜሪካኖች አይደሉም።የሱዳንን ሕዝብ «ወንድም» የሚሉት፣ከአብዛኛዉን ሱዳናዊ ጋር ቋንቋ፣ ባሕል፣ ኃይማኖት የሚጋሩት አረቦች እንጂ።ሳዑዲ አረቢያ፣ ግብፅና የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች በጋራ መግለጫዉ ይዘት ላይ አልተስማሙም።...more13minPlay
April 21, 2025አዲሱ የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ካቢቤና ተቃውሞውበአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራ የህወሓት ክንፍ የጀነራል ታደሰ ወረደ አዲሱ ካቢኔ አካታች አይደለም በማለት ተችቷል። በአቶ ጌታቸው የሚመራው የህወሓት ክንፉ እንዳለው አዲሱ የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ጀነራል ታደሰ ወረደ፥ ለአንድ ቡድን ብቻ በማዳላት አካታች ያልሆነ ካቢኔ መስርተዋል ያለ ሲሆን ይህ እንዲስተካከልም ጥሪ አቅርቧል።...more4minPlay
April 21, 2025የሮማ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ርዕሠ-ሊቀነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ዜና ዕረፍትየሮማ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ርዕሠ-ሊቀነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ዛሬ ጠዋት በ88 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በአጸደ ሥጋ ተለዩ።...more0minPlay
April 20, 2025እንወያይ፤ የኢትዮጵያ የመናገር ነጻነት ወዴት እያመራ ነው?በጋዜጠኞችና የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች የሚደርሱ እስርና ወከባዎች በኢትዮጵያ በቋፍ ላይ የነበረውን የፕረስ ነጻነት አደጋ ላይ እንደጣለው የሙያው ባለቤቶችና ተከራካሪዎች በየጊዜው ስጋታቸውን እየገለጹ ይገኝሉ። በሙያው የተሰማሩ ጋዜጠኞች የሙያዊ ክህሎትና የሥነምግባር ችግሮች እንደሚስተዋሉም በመስኩ የተደረጉ ጥናቶች ያመላክታሉ።...more46minPlay
April 18, 2025አንድ - ለ - አንድ፣ ኢትዮጵያ «የኃይል እጥረት የለም፣ መብራት ግን ይቆራረጣል» ባለሙያየዉሐ ሐብት አስተዳደር፤ የድንበር ተሻጋሪ ወንዞች፣ የሐድሮ ዲፕሎማሲ ባለሙያ አማካሪ ናቸዉ።ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ ያስገነባችዉ ግዙፍ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ የሕዳሴ ግድብ የዓለም ርዕስ በነበረበት ዘመን በኢትዮጵያ የዉኃ ሐብት፣ የመስኖና የኃይል ሚንስቴር የድንበር ተሻጋሪ ወንዞች ጉዳይ ኃላፊ ነበሩ።...more20minPlay
April 17, 2025የፖለቲካ ፓርቲ አባል የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን የቦርድ አባል መሆኑን የሚፈቅድ አዋጅ ፀደቀበሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አዋጅ ቁጥር 1238/2013 የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን የዕለት ተዕለት ሥራውን እንዳያከናዉን ለተቋሙ ቦርድ የተሰጠው ሥልጣን "የሕግ ክፍተት ያለበት በመሆኑ" እና ያንን ለተቋሙ ሥራ አስፈፃሚ መመለስ አስፈላጊ በመሆኑ ማሻሻል እንዳስፈለገ ገልጿል።...more4minPlay
April 16, 2025“ትምህርት ቤቶችን የግጭት ሰለባ የምናደርግበትን መንገድ ማቆም አለብን” የኢትዮጵያ የትምህርት ሚኒስትር ብርሀኑ ነጋከትምህርት የቀሩ 7.2 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ልጆች ጉዳይ “በጣም ሊያሳስብ” እንደሚገባ የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሀኑ ነጋ ተናገሩ። “ትምህርት ቤቶችን የግጭት ሰለባ የምናደርግበትን መንገድ ማቆም አለብን” ብለዋል። የኑሮ ውድነት ለበረታባቸው አስተማሪዎች የሚቋቋመው የመምህራን የኅብረት ሥራ ባንክ በ2018 ሥራ ሊጀምር እንደሚችል ተስፋ አላቸው።...more0minPlay
April 15, 2025አዲስ መንግስት የሚመሰርቱት የጀርመን ወግ አጥባቂና የመሀል ግራ ፓርቲዎች የተስማሙበት ውል«መደበኛ ያልሆነ ስደትን እናስቆማለን፣ ድንበሮች ላይ ቁጥጥር ይደረጋል፤ የጥገኝነት ማመልከቻዎችንም ውድቅ እናደርጋለን፣ ወደ አገራቸው የመመለስ እርምጃዎችን እንወስዳለን ። በፈቃደኝነት ስደተኞችን የማስገባት መርሀግብርን እናቆማለን የቤተሰብ አባላትን እንደገና ማገናኘትን እናቋርጣለን» የጀርመን መራኄ መንግስት እንደሚሆኑ የሚጠበቁት ፍሪድሪሽ ሜርስ...more11minPlay
FAQs about DW | Amharic - News:How many episodes does DW | Amharic - News have?The podcast currently has 2,914 episodes available.