Sign up to save your podcastsEmail addressPasswordRegisterOrContinue with GoogleAlready have an account? Log in here.
በሣምንታዊው የከኤኮኖሚው ዓለም መሰናዶ የኢትዮጵያ፣ አፍሪካ እና ዓለምን ምጣኔ ሐብታዊ ይዞታ የተመለከቱ ትንታኔዎች፣ ቃለ መጠይቆች እና ዘገባዎች ይቀርባሉ። ይኸ መሰናዶ ሀገራት የሚያወጧቸውን ኤኮኖሚያዊ ፖሊሲዎች፣ መሪዎች የሚወስዷቸውን ምጣኔ ሐብታዊ ውሳኔዎች በመፈተሽ ጥቅም እና ጉዳታቸውን ያቀርባል።... more
FAQs about ከኤኮኖሚው ዓለም:How many episodes does ከኤኮኖሚው ዓለም have?The podcast currently has 100 episodes available.
December 11, 2024የሪል እስቴት ልማት እና የማይንቀሳቀስ ንብረት ግብይትና ግመታ አዋጅ ምን ይዞ መጣ?የሪል እስቴት ልማት እና የማይንቀሳቀስ ንብረት ግመታን አጣምሮ የያዘው አዋጅ “ብዙ የሚያሻሙ” ነገሮች ቢኖሩትም ባለሙያዎች “ገበያውን ቅርጽ ያስይዘዋል” ብለው ይጠብቃሉ። አዋጁ ያለ ደንበኛው ፈቃድ “ቢያንስ 80% ያልተጠናቀቀ ቤት” ማስተላለፍ ይከለክላል። በዘርፉ የሚደረገው ግብይት በባንክ ወይም በኤሌክሮኒክ የክፍያ ዘዴ ብቻ እንዲሆን ተወስኗል።...more11minPlay
December 04, 2024የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሪፖርት ምን ያሳያል?በ2017 የመጀመሪያ መንፈቅ የወጪ ንግድ በ81% ማደጉን የብሔራ ባንክ ሪፖርት ያሳያል። የንግድ ሚዛን ጉድለት እየቀነሰ በመሔዱ የሀገሪቱ የክፍያ ሚዛን ተሻሽሎ ትርፍ 573 ሚሊዮን ዶላር መድረሱን ይጠቁማል። የሐምሌው የውጪ ምንዛሪ ግብይት ሥዓት ለውጥ በዶላር የክፍያ ግዴታ በነበረባቸው ባንኮች ላይ ስላደረሰው ኪሳራ ግን ምንም አላለለም።...more10minPlay
November 20, 2024የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደረሰኝ ቁጥጥር ለምን ከመርካቶ ተቃውሞ ገጠመው?የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በመርካቶ አስመጪዎች፣ አከፋፋዮች እና ቸርቻሪዎች ደረሰኝ መቁረጣቸውን ለማረጋገጥ የጀመረው ቁጥጥር ከገበያው ተዋናዮች ተቃውሞ ገጥሞታል። ቁጥጥሩ ከተጀመረ በኋላ ባለፉት ሣምንታት በመርካቶ የንግድ መደብሮች ተዘግተው ነበር። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ2017 የመጀመሪያ መንፈቅ የሰበሰበው ገቢ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት አኳያ በ12 ቢሊዮን ብር ከፍ ቢልም ከዕቅዱ በ10 ቢሊዮን ብር ገደማ ዝቅ ያለ ነው።...more9minPlay
November 13, 2024የጀርመን ጥምር መንግሥት ሲፈርስ ሀገሪቱ የተጣለባት የብድር ገደብ ሚና ምንድነው?ጀርመን በምትመራበት መሠረታዊ ሕግ ከአጠቃላይ ዓመታዊ የምርት መጠን (GDP) ከ0.35 በመቶ በላይ እንዳትበደር ገደብ ተጥሎባታል። የሀገሪቱ ኤኮኖሚን ለማነቃቃት ገደቡ እንዲነሳ በሚሹት መራኄ መንግሥት ኦላፍ ሾልስ እና አይሆንም የሚል አቋም በነበራቸው በቀድሞው የፋይናንስ ሚኒስትር ክርስቲያን ሊንድነር መካከል በተፈጠረ አለመግባባት የጀርመን ጥምር መንግሥት ፈርሷል።...more10minPlay
November 06, 2024የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ዕዳ ክፍያ በኢትዮጵያውያን ትከሻ ላይ ተጫነ?ገንዘብ ሚኒስቴር የመንግሥት የልማት ድርጅቶችን 845.3 ቢሊዮን ብር የንግድ ባንክ ዕዳ ከነወለዱ ለመክፈል ተረክቧል። መንግሥት ንግድ ባንክን ለመታደግ በተከተለው አካሔድ ትምህርት እና ጤና የመሳሰሉ አገልግሎቶች ለመሥራት የሚያስፈልገውን ገንዘብ ለዕዳ ክፍያ ሊያውል አሊያም ገቢውን ለማሳደግ ተጨማሪ ግብር ሊያስከፍል እንደሚችል ባለሙያዎች ይናገራሉ።...more12minPlay
October 30, 2024ኢትዮጵያውያን የአፍሪካ ኮምት ተሳታፊዎች በጀርመን በቀሰሙት ልምድ ሀገራቸውን ለመጥቀም ተስፋ ሰንቀዋልአራት ኢትዮጵያውያን አፍሪካ ኮምት በተባለው እና በጎርጎሮሳዊው ከ2023 እስከ 2025 በሚዘልቀው መርሐ-ግብር በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ። ይኸ መርሐ-ግብር አፍሪካውያን ወጣት ባለሙያዎችን ከሥመ -ጥር የጀርመን ኩባንያዎች የሚያገናኝ ነው። ገነት አታክልት እና ጌቱ ታደለ በሁለት ግዙፍ የጀርመን ኩባንያዎች ውስጥ ለስምንት ወራት እየሰሩ ሲማቁ ቆይተዋል።...more12minPlay
October 23, 2024በኢትዮ-ቴሌኮም መደበኛ የአክሲዮን ሽያጭ ልብ መባል ያለባቸው ጉዳዮች የትኞቹ ናቸው?የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ የኢትዮ-ቴሌኮምን መደበኛ አክሲዮን ሽያጭ ከጀመረ በኋላ የኩባንያውን ያለፈ ዓመት ገቢ እና ትርፍ በማስላት “ያዋጣል” ወይስ “አያዋጣም” የሚሉ ትንታኔዎች በማኅበራዊ ድረ-ገጾች እና በመገናኛ ብዙኃን እየታዩ ነው። መንግሥት ከመደበኛ አክሲዮኖች ሽያጭ 30 ቢሊዮን ብር (255 ሚሊዮን ዶላር) የማግኘት ዕቅድ ያለው ሲሆን ወደፊት የኢትዮ-ቴሌኮም 45 በመቶ ድርሻ ለውጪ ባለወረቶች ይሸጣል ተብሎ ይጠበቃል። ለመሆኑ ልብ መባል ያለባቸው ጉዳዮች የትኞቹ ናቸው? ባለሙያዎችስ ምን ይመክራሉ?...more11minPlay
October 16, 2024የኢትዮጵያ ባንኮች የውጪ ምንዛሪ መሸጫ እና መግዣ ተመን ልዩነት ወደ 2% ቢያጠቡም የሚያስከፍሉትን ኮሚሽን አላሳወቁምየኢትዮጵያ ባንኮች በውጪ ምንዛሪ መግዣ እና መሸጫ ተመኖቻቸው መካከል ያለውን ልዩነት የብሔራዊ ባንክን የፖሊሲ ለውጥ ተከትሎ ወደ 2 በመቶ ዝቅ አድርገዋል። እርምጃው የባንኮች የዶላር የመሸጫ ተመን ከ6 እስከ 10 ብር እንዲቀንስ አድርጎታል። ይሁንና ባንኮቹ በተቆጣጣሪው በታዘዙት መሠረት ለደንበኞቻቸው ከውጪ ምንዛሪ ጋር የተያያዙ አገልግሎቶች ሲያቀርቡ የሚጠይቁትን ክፍያ እና ኮሚሽን ይፋ አላደረጉም።...more11minPlay
FAQs about ከኤኮኖሚው ዓለም:How many episodes does ከኤኮኖሚው ዓለም have?The podcast currently has 100 episodes available.