Sign up to save your podcastsEmail addressPasswordRegisterOrContinue with GoogleAlready have an account? Log in here.
በሣምንታዊው የከኤኮኖሚው ዓለም መሰናዶ የኢትዮጵያ፣ አፍሪካ እና ዓለምን ምጣኔ ሐብታዊ ይዞታ የተመለከቱ ትንታኔዎች፣ ቃለ መጠይቆች እና ዘገባዎች ይቀርባሉ። ይኸ መሰናዶ ሀገራት የሚያወጧቸውን ኤኮኖሚያዊ ፖሊሲዎች፣ መሪዎች የሚወስዷቸውን ምጣኔ ሐብታዊ ውሳኔዎች በመፈተሽ ጥቅም እና ጉዳታቸውን ያቀርባል።... more
FAQs about ከኤኮኖሚው ዓለም:How many episodes does ከኤኮኖሚው ዓለም have?The podcast currently has 117 episodes available.
April 30, 2025የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ማሻሻያ መርሐ-ግብር የሚመሩ ሹማምንት በዋሽንግተን ምን አሉ?የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት እና የዓለም ባንክ የጸደይ ጉባኤ በዋሽንግተን ሲካሔድ ጎን ለጎን የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት መንግሥታቸው ተግባራዊ ስለሚያደርገው የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና ውጤቶቹ ማብራሪያ ሲሰጡ ሰንብተዋል። ኢትዮጵያ የዕዳ አከፋፈል ሽግሽግ እየጠበቀች ለመሠረተ-ልማት ግንባታ አማራጭ የገንዘብ ምንጭ እያፈላለገች ነው።...more11minPlay
April 23, 2025የትራምፕ ታሪፍ የዓለምን ኢኮኖሚ ዕድገት እንዳቀዛቀዘ ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት ትንበያ አሳየዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት ለዓለም ዋና ዋና ኢኮኖሚዎች በጥር የሰጠውን የዕድገት ትንበያ የዶናልድ ትራምፕ ታሪፍ ባስከተለው ውጥረት ምክንያት ከልሷል። ተቋሙ የኢትዮጵያ አጠቃላይ ሀገራዊ ምርት በ6.6% ያድጋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ይፋ አድርጓል። ትንበያው የኢትዮጵያ መንግሥት በ2017 ከሚጠብቀው ኢኮኖሚያዊ ዕድገት በ1.8 በመቶ ዝቅ ያለ ነው።...more11minPlay
March 26, 2025የኢትዮጵያ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ለዕዳ ሽግሽግ ድርድር እንዲዘጋጁ ገንዘብ ሚኒስቴር አሳሰበገንዘብ ሚኒስቴር “ዋና ዋና” ላላቸው የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ከአበዳሪ መንግሥታት ጋር ለሚደረግ የመግባቢያ ሥምምነት ድርድር እንዲዘጋጁ ማሳሰቢያ ሰጥቷል። የገንዘብ ሚኒቴር ተቋማቱ እንዲዘጋጁ ያሳሰበው ኢትዮጵያ አበዳሪዎቿን ከሚወክለው ኮሚቴ ጋር የ8.4 ቢሊዮን ዶላር ገደማ ዕዳ ለማሸጋሸግ “በመርኅ ደረጃ” ሥምምነት ላይ ከደረሰች በኋላ ነው። ከአበዳሪዎች ኮሚቴ ጋር የተደረሰው ሥምምነት በጎርጎሮሳዊው አቆጣጠር ከ2023 እስከ 2028 ባሉት ዓመታት ለኢትዮጵያ 2.5 ቢሊዮን ዶላር ገደማ የዕዳ ክፍያ እፎይታ ይሰጣል።...more11minPlay
March 19, 2025ለኢትዮጵያ ከዓለም የንግድ ድርጅት አባልነት ምን አለ?የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ሀገራት በቡድን ከኢትዮጵያ ልዑካን ጋር የተደራደሩበት አምስተኛ ስብሰባ ዛሬ በጄኔቫ ተካሒዷል። ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን የጀመረችውን ሒደት ለማጠናቀቅ ወደ ጄኔቫ የተመለሰችው “በተቋሙ ላይ ከፍተኛ ጥያቄ” በሚነሳበት ወቅት ነው። ባለፉት ዓመታት የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ሀገራት ብሔራዊ ጥቅሞቻቸውን ለማስጠበቅ እና ተገዳዳሪዎቻቸውን ለመቅጣት የድርጅቱን ሕግጋት እየጣሱ መሔዳቸውን ባለሙያዎች ታዝበዋል።...more11minPlay
March 12, 2025የአፍሪካ መንግሥታት የናጠጡ ባለጠጎችን የሐብት ግብር ማስከፈል አለባቸው?በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ብርቱ የኢኮኖሚ ፈተናዎች እየገጠሟቸው ነው። መንግሥታት የተሻለ የጤና አገልግሎት ለማቅረብ፣ ትምህርት ቤቶች፣ መንገዶች እና ሌሎች መሠረተ-ልማቶች ለመገንባት የሚያስፈልጋቸውን ገንዘብ ለማግኘት ሲቸገሩ የአፍሪካ ሀገራት በየጊዜው እየጨመረ በሚሔድ የዕዳ ጫና እየቃተቱ ነው። ላለፉት በርካታ ዓመታት የአፍሪካ መንግሥታት በአማካይ ለጤና አገልግሎት ከመደቡት የበለጠ ለዕዳ ክፍያ ወጪ አድርገዋል። በአኅጉሪቱ የናጠጡ ባለጠጎች ቁጥር ሲጨምር የሐብት ግብር ማስከፈል እንዲጀመር የሚደረጉ ጥሪዎችም ከፍ ብለው መሰማት ጀምረዋል።...more10minPlay
March 05, 2025የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በብድር ወለድ ምጣኔ ማሻሻያ ፊቱን ወደ ገበያ ተመን አዞረለዓመታት ለመንግሥት “ርካሽ” ብድር ሲሰጥ የቆየው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መሠረታዊ የወለድ ምጣኔ ማሻሻያ ተግባራዊ ሲያደርግ ፊቱን ወደ ገበያ ተመን አዙሯል። ንግድ ባንክ ከዚህ ቀደም ከውጪ ምንዛሪ ግኝት ጋር በተያያዘ ቅድሚያ ለሚሰጣቸው ደንበኞቹ የሚያቀርባቸውን ጥቅማ ጥቅሞች በመተው ለወጪ ንግድ በሚሰጠው ብድር የሚያስከፍለውን ወለድ አሳድጓል። በማሻሻያው የግብርና ብድር ወለድ በመጠኑ ሲቀንስ የኮንዶሚኒየም የመኖሪያ ቤቶች በነበረበት ቀጥሏል። ንግድ ባንክ ከአርብ ጀምሮ ለቤት መግዣ በ14 በመቶ ለተሽከርካሪ በ15 በመቶ ወለድ ያበድራል።...more11minPlay
February 19, 2025የኢትዮጵያ ቦንድ ባለቤቶች የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅትን ሪፖርት ለምን ተቃወሙ?ኢትዮጵያ የገጠማት የዕዳ ጫና የመክፈያ ጊዜ በማራዘም የሚፈታ የአጭር ጊዜ የገንዘብ እጥረት ወይስ የተለቃችውን ብድር ለመቀነስ የሚያስገድድ የመክፈል ችግር? ጉዳዩ መንግሥት የኢንዱስትሪ ፓርኮች ለማስፋፋት እና ስኳር ፋብሪካዎች ለመገንባት ሲነሳ አንድ ቢሊዮን ዶላር ያበደሩ የግል ኢንቨስተሮችን ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት ሪፖርት እያወዛገበ ነው።...more10minPlay
February 12, 2025ኢትዮጵያ የመረጠችው የሊብራል ኢኮኖሚ ሥርዓት ውጤታማ እንዲሆን የሚያስችል ከባቢ አለ?ኢትዮጵያ በታሪኳ ከየትኛውም ጊዜ በላይ አሁን የበለጠ ወደ ሊብራል የኢኮኖሚ ሥርዓት ማዘንበሏን ባለሙያዎች ይስማማሉ። ሊብራል የኤኮኖሚ ሥርዓት ግለሰቦች ያለ መንግሥት ጣልቃ ገብነት በነጻ እንዲገበያዩ የሚፈቅድ ነው። ሊብራል ኤኮኖሚ በኢትዮጵያ ውጤታማ እንዲሆን የሚያስችል የፖለቲካ ሥርዓት እና ጠንካራ የግል ዘርፍ አለ?...more11minPlay
February 05, 2025የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ታሪፍን እንደ መሣሪያ የመጠቀም ሥልት የዓለም የንግድ ሥርዓትን አስግቷልየአሜሪካ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ የሀገራቸዉን የንግድ ጉድለት ለማሟላት እና ፖለቲካዊ ጉዳዮቻቸውን ለማስፈጸም ታሪፍን እንደ መሣሪያ እየተጠቀሙ ነው። አሜሪካ ከሜክሲኮ እና ከካናዳ በምትሸምታቸው ሸቀጦች ላይ 25 በመቶ ታሪፍ እንዲጣል ትራምፕ ያስተላለፉት ውሳኔ ለ30 ቀናት እንዲቆም ተደርጓል። በቻይና ላይ የተጣለው ታሪፍ ሥራ ላይ የዋለ ሲሆን የፕሬዝደንት ሺ ዢፒንግ መንግሥት በአጸፋው በአሜሪካ ሸቀጦች ላይ ተመሣሣይ እርምጃ ወስዷል። ቻይና ጉዳዩን ወደ የዓለም የንግድ ድርጅት እንደምትወስድ ዝታለች። የዓለም የንግድ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ንጎዚ ኦኮንጆ ኢዌላ የታሪፍ ውጥረት የፈጠሩ ሀገራት አደብ እንዲገዙ ጥሪ አቅርበዋል።...more10minPlay
FAQs about ከኤኮኖሚው ዓለም:How many episodes does ከኤኮኖሚው ዓለም have?The podcast currently has 117 episodes available.