Sign up to save your podcastsEmail addressPasswordRegisterOrContinue with GoogleAlready have an account? Log in here.
ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና ዜናዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ። የዶይቼ ቬለን ዜናዎች በአፕል ፖድካስት... more
FAQs about የዓለም ዜና:How many episodes does የዓለም ዜና have?The podcast currently has 679 episodes available.
May 29, 2025የግንቦት 21 ቀን 2017 ዓ ም የዓለም ዜና*የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኢሳያስ አፈወርቂ ወቀሳ ላይ ምላሽ ሰጠ*የግብፁ ፕሬዚዳንት አልሲሲ ብርቱ ተፎካካሪ ከስር ተፈቱ* ናይጄሪያ ውስጥ በሁለት አመታት ውስጥ ከ 10 000 በላይ ሰዎች ተገደሉ*«እስራኤል በጋዛ የጦር ወንጀል እየፈፀመች ነው» የቀድሞ የእስራኤል ጠ/ሚነስትር*ኤሎን ማስክ ለትራምፕ መስራታቸውን ሊያቆሙ ነው*የዩናይትድ ስቴትስ ለአለም አቀፍ ተማሪዎች ቪዛ ላለመስጠት መወሰኗ ቁጣ ቀሰቀሰ...more11minPlay
May 28, 2025የግንቦት 20 ቀን 2017 ዓ.ም. የዓለም ዜናየደርግ ሥርዓት ከኢትዮጵያ የመንግሥት ሥልጣን ከተወገደ ዛሬ 34 ዓመቱን ደፈነ። ከሦስት አስርት ዓመታት በላይ በብሔራዊ በዓልነት ይታሰብ የነበረው ግንቦት 20 በሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎች መደበኛ የሥራ ቀን ሆኖ ሲያልፍ ትግራይ ክልል ግን በደመቀ ሥርዓት ተከብሯል። ፖርት ሱዳንን ጨምሮ በሱዳን ጦር ኃይል የተያዙ አካባቢዎች ላይ የሰው አልባ አውሮፕላን ጥቃት መፈጸሙ ተዘገበ። የኢራን አብዮታዊ ዘብ አዛዥ ዩናይትድ ስቴትስን አስጠነቀቁ። የፈረንሳይ ፍርድ ቤት በአብዛኛው ለአካለ መጠን ያልደረሱ ሕጻናትን ጨምሮ ወደ 300 ገደማ ህሙማን ላይ በደል በፈጸመ የቀዶ ህክምና ባለሙያ ላይ የ20 ዓመት እስራት ፈረደ።...more10minPlay
May 27, 2025የዓለም ዜና፤ ግንቦት 19 ቀን 2017አርስተ ዜና የጀርመኑ መራሔ መንግሥት ፍሬድሪክ ሜርስ ስራኤል በጋዛ እየፈፀመች ያለዉ ድርጊት «ትክክል ያልሆነ» ሲሉ ወቀሱ። በሌላ በኩል ጀርመንን ጨምሮ ቁልፍ ምዕራባዉያን የዩክሪን ደጋፊዎች ለዩክሪን በሚልኩት የጦር መሳርያ ላይ የተጣለ ገደብን አነሱ።--በእነአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራ ዴሞክራሲያዊ ስምረት ትግራይ የተሰኘ አዲስ የፖለቲካ ፓርቲ በምርጫ ቦርድ ግዚያዊ የምዝገባ ፍቃድ አገኘ።--በጦርነት በተመሰቃቀለችዉ ሱዳን በኮሌራ በሽታ የተያዘዉ ሰዉ ቁጥር መጨመሩን የጤና ጥበቃ ሚ/ር አስታወቀ።--የሩሲያ ወታደራዊ አውሮፕላኖች የፊንላንድ የአየር ክልልን ጥሰዋል ከተባለ በኋላ ፊንላንድ የሩሲያን አምባሳደር ለጥያቄ ጠራች።...more12minPlay
May 26, 2025የግንቦት 18 ቀን 2017 ዓ.ም. የዓለም ዜናበጋምቤላ ክልል ዲማ ወረዳ ታጣቂዎች በአንድ አውቶብስ ላይ ባደረሱት ጥቃት አምስት ሰዎች ተገደሉ። ሌሎች ስድስት ሰዎችም ተጎድተዋል። ጥቃት አድራሾቹ ከደቡብ ሱዳን የመጡ የሙርሌ ታጣቂዎች መሆናቸው ተገልጿል።የግሪክ ባሕር ኃይል ከ500 በላይ ስደተኞችን ከመስመጥ ማዳኑን የሀገሪቱ ባለሥልጣናት ገለጹ።ዩጋንዳ ከጀርመን ጋር መከላከያን በተመለከተ ያላትን ትብብር ማቋረጧን አስታወቀች። የእስራኤል መንግሥት በቅርቡ ጋዛ ላይ የተኩስ አቁም እንዲደረግ የቀረበለትን ጥያቄ ውድቅ ማድረጉ ተነገረ። ሃገራት እስራኤል ጋዛ ላይ የምትወስደውን የኃይል እርምጃ እንድታቆም እየጠየቁ ነው።...more9minPlay
May 25, 2025DW Amharic የግንቦት 17 ቀን 2017 የዓለም ዜናበኢትዮጵያ “ኤምፖክስ” ተብሎ በሚጠራው የጦጣ ፈንጣጣ የተያዘ ሰው መገኘቱን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ የኤርትራ መንግሥት እና ሕዝብ ለኢትዮጵያ “ተሐድሶ ወይም ለውጥ በከፍተኛ ተስፋ ባደረጉት ያልተቆጠበ ድጋፍ ድንገት በተፈጠሩ ክስተቶች ምክንያት እንደማይቆጩ” ተናገሩ። በጋዛ በአንድ ቀን 38 ሰዎች በእስራኤል ጥቃቶች መገደላቸውን የሐማስ የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። ሩሲያ እና ዩክሬን በሦስት ዙር ያካሔዱትን የጦር ምርኮኞች ልውውጥ አጠናቀቁ። የጀርመን የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር አሌክሳንደር ዶብሪንት የተወሰኑ ስደተኞች ቤተሰቦቻቸውን ወደ ጀርመን ከማምጣት የሚከለክል ሕግ እየተዘጋጀ መሆኑን አረጋገጡ።...more9minPlay
May 24, 2025DW Amharic የግንቦት 16 ቀን 2017 የዓለም ዜናአፍሪካ በማዕድናት፣ በሚታረስ መሬት እና በኢንዱስትሪ ያላትን እምቅ ሀብት ለዛሬውም ሆነ ለወደፊቱ ትውልድ ሲባል መጠበቅ እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር አሳሰቡ። ፕሬዝደንት ኢስማኤል ዑመር ጉሌሕ በሚያዝያ 2018 በሚካሔደው የጅቡቲ ምርጫ ሊወዳደሩ እንደሚችሉ በገደምዳሜ ፍንጭ ሰጡ። በኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ ማኪና በተባለ አካባቢ በተቀሰቀሰ የእሳት ቃጠሎ ቢያንስ ስምንት ሰዎች ሕይወታቸውን አጡ። በእስራኤል ጥቃት የተገደሉ የ79 ሰዎች አስከሬኖች ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ ወደ ሆስፒታሎች መድረሳቸውን የጋዛ የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።...more9minPlay
May 23, 2025የዐርብ ግንቦት 15፣ ቀን 2017 ዓ.ም የዓለም ዜናቤኒሻንጉል፥ በካማሺ ዞን ምዥጋ ወረዳ የታጣቂዎች ጥቃት፤ ለንደን፥ አምነስቲ ኢንተርናሽናል፦ የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ከጤና ባለሞያዎች ጋር በአሰቸኳይ ሊነጋገሩ ይገባል አለ፤ አአ፥ ዩናይትድ ስቴትስ ኢትዮጵያ ውስጥ ሕዝቡን እየጎዳ ላለው ግጭት መፍትሄ እንዲፈለግ አሳሰበች፤ ጋምቤላ፥ ኢትዮጵያ የሚገኙ የደቡብ ሱዳን ስደተኞች «የጤና ቀውስ» የማይቀር ነው ተባለ፤ ዋሽንግተን፥ ትራምፕ የአውሮጳ ኅብረት ሸቀጦች ላይ የ50 በመቶ ቀረጥ ሊጥል ነው፤ ዩክሬን እና ሩስያ ከዚህ ቀደሙ ከፍተኛ የሆነ የእስረኛ ልውውጥ አደረጉ ።...more10minPlay
May 22, 2025የግንቦት 14 ቀን 2017 ዓ,ም የዓለም ዜናየኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ከደመወዝ ጭማሪ ጋር በተገናኘ የህክምና ባለሙያዎች ለሚወስዱት እርምጃ የሚሰጠው ምላሽ ወደ መብት ጥሰት ማምራት እንደሌለበት አሳሰበ። በአሜሪካ የእስራኤል ኤምባሲ ሁለት ሠራተኞች ዋሽንግተን ዲሲ ላይ መገደላቸው የተለያዩ ሃገራትን ውግዝት አስከተለ። እስራኤል መንስኤው ጸረ ሴማዊነት ነው ብላለች። የእስራኤል መንግሥት ዶሀ ቀጠር በመካሄድ ላይ ከሚገኘው የጋዛ የተኩስ አቁም ድርድር መውጣቱ እየተነገረ ነው። የጀርመን አቀብያነ ሕግ የሁቲ አማፂ ቡድን አባል ሳይሆን አቅርም በሚል ተጠረጠረ ግለሰብን በዛሬው ዕለት በቁጥጥር ሥር ማዋላቸውን ገለጹ።...more10minPlay
May 21, 2025የግንቦት 13 ቀን 2017 የዓለም ዜና-በኦሮሚያ ክልል ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዉስጥ የኤሌክትሪክ ኃይልና ዉኃ ለተከታታይ ሳምንታት በመቋረጡ ሕዝብ ለችግር መጋለጡን ነዋሪዎች አስታወቁ።ዉኃና መብራቱ የተቋረጠዉ አንድ የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ በመቃጠሉ እንደሆነ ባለሥልጣናት አስታዉቀዋል።---የእስራኤል መንግሥት የጋዛ ፍልስጤሞችን መግደል፣ማሰቃየትና ማስራቡን እንዲያቆም የሚደረግበት ግፊት እንደቀጠለ ነዉ።የእስራኤል ወታደሮች የምዕራባዊ ዮርዳኖስ ወንዝ ዳርቻን በሚጎበኙ ዲፕሎማቶች ላይ ተኩስ መክፈታቸዉን አዉሮጶች አዉግዘዉታል።---የሩሲያዉ ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን ጦራቸዉ በቅርቡ መልሶ የተቆጣጠራትን የኩርስክ ግዛትን ጎበኙ።...more12minPlay
FAQs about የዓለም ዜና:How many episodes does የዓለም ዜና have?The podcast currently has 679 episodes available.