የግንቦት 28 ቀን 2016 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና
ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጋር በተያያዘ ከታሰሩ ከ 80 በላይ ሰዎች ፍርድ ቤት ቀረቡ። ዛሬ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት ከቀረቡት ውስጥ ጋዜጠኞች፣ የቤተ ክርስትያን ሰዎች እና ፖለቲከኞች ይገኙበታል ተብሏል።
የዘንድሮው የዶቼቬለ የንግግር ነጻነት ሽልማት ለሩስያዊቷ ዩልያ ናቫልናያና ሟቹ ባለቤታቸው አሌክሲ ናቫልኒ ለመሠረቱት በምህፃሩ FBK ለተባለው ፀረ ሙስና ድርጅታቸው ዛሬ ተሰጠ።
አንድ «አማራጭ ለጀርመን» የተባለው የጀርመን ፓርቲ ፖለቲከኛ በደቡብ ምዕራብ ጀርመንዋ በማንሀይም ከተማ ትናንት ጥቃት እንደተፈጸመባቸው ፓርቲያቸውና ፖሊስ አስታወቁ።