የሐሙስ ሰኔ 20 ቀን 2016 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና
የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ህዝባቸው የተቃወመው የታክስ ጭማሪ ሕግ ላይ ፊርማቸውን እንደማያኖሩ ቢያሳውቁም ተቃዋሚዎች ዛሬም አደባባይ ወጥተው ነበር። በናይሮቢ የንግድ ማዕከል የተሰባሰቡ በርካታ ተቃዋሚዎችን ፖሊስ በፕላስቲክ ጥይቶችና በአስለቃሽ ጢስ በትኗል።
በሱዳን 755 ሺህ ሰዎች ለረሀብ መጋለጣቸውን ዓለም አቀፍ አጥኚዎች ዛሬ ይፋ ያደረጉት አንድ ዘገባ አስጠነቀቀ። ረሀቡ የሚያሰጋው በ14 የሱዳን አካባቢዎች ነው።
ከከሸፈው የትናንትናው የቦሊቭያ መፈንቅለ መንግሥት ሙከራ በኋላ በርካታ ወታደራዊ መኮንንኖች መታሰራቸውን አንድ ከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣን ተናገሩ።