Sign up to save your podcastsEmail addressPasswordRegisterOrContinue with GoogleAlready have an account? Log in here.
ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና ዜናዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ። የዶይቼ ቬለን ዜናዎች በአፕል ፖድካስት... more
FAQs about የዓለም ዜና:How many episodes does የዓለም ዜና have?The podcast currently has 746 episodes available.
August 31, 2024የነሐሴ 25 ቀን 2016 ዓ.ም የዓለም ዜና*ኢትዮጵያ ፦ በአማራ ክልል ከፍተኛ ዝናብ ያስከተለው ጥፋት*ኬንያ፣ ከፍተኛ የኃይል መቆራረጥ ገጠማት*ቱኒዝያ፣ አደጋ ላይ የነበሩ 28 ስደተኞች ተረፉ*ጀርመን፤ ስድስት ሰዎች በስለት ተወግተው ቆሰሉ*እስራኤል፤ በጄኒን የሚካሄደው ከባድ ውጊያ ቀጥሏል*ኢትዮጵያ ፤ በዓለም ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና 2ኛ ደረጃ ላይ...more9minPlay
August 30, 2024የነሐሴ 24 ቀን 2016 ዓ.ም የዓለም ዜናበማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ማረቆ ልዩ ወረዳ ማንነትን መሠረት ያደረገ ነው በተባለ ጥቃት አራት የአንድ ቤተሰብ አባላትን ጨምሮ ሰባት ሰዎች መገደላቸው ተሰማ። ኢትዮጵያ ሶማሊላንድ ውስጥ ለሚገኘው ቆንስላ ጽሕፈት ቤቷ አዲስ አምባሳደር ሾመች። የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት የኢትዮጵያን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ ከ3,600 በላይ የሕግ ታራሚዎችን በይቅርታ መልቀቁን አስታወቀ። ከታሰሩ የኦነግ አባላት የተለቀቀ የለም። የቀድሞው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ፕሮፌሰር እንድርያስ እሸቴ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ትናንት ሐሙስ ነሐሴ 23 ቀን፣ 2016 ዓ.ም ማረፋቸውን ዩኒቨርስቲው አስታወቀ።...more10minPlay
August 29, 2024የዓለም ዜና፤ ነሐሴ 23 ቀን፤ 2016 ዓ.ም ሐሙስአርስተ ዜና፤ --የአውሮጻ ህብረት የውጭ ጉዳይ ሃላፊ ጆሴፍ ቦሬል በእስራኤል ሚኒስትሮች ላይ ማዕቀብ እንዲጣል ሃሳብ ለማቅረብ እየሰሩ እንደሆነ ተመለከተ። --በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስልጢ ዞን ጎርፍ ከ6ሺህ በላይ ነዋሪዎችን አፈናቀለ። የጎርፍ አደጋው መንሥኤ በአካባቢው ከተገነባ የመስኖ ግድብ ነዉ ተብሏል። በሌላ በኩል በሰሜን ጎንደር ዞን ጠለምት ወረዳ በናዳ ለተጎዱ እርዳታ እየተጠበቀ ነዉ። --ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት «ሂውማን ራይትስ ዋች» በሱዳን ከ16 ወራት በላይ በዘለቀዉ የእርስ በእርስ ግጭት፤ ሁለቱንም ተፋላሚ ወገኖች ፤ የጦርነት ወንጀል ፈፅመዋል ሲል ከሰሰ።...more11minPlay
August 28, 2024የዓለም ዜና፣ ነሐሴ 22፣ 2016-የኢትዮጵያ መንግሥትን በነፍጥ የሚወጉ ኃይላት በሐገሪቱ ብሔራዊ የምክክር ሒደት እንዲካፈሉ ለተደረገላቸዉ ጥሪ መልስ አለመስጠታቸዉን የምክክር ኮሚሽን አስታወቀ።ለታጣቂዎቹ ኃይላት ጥሪዉ የተደረገበትን መንገድና ጥሪዉ ሥለመድረስ አለመድረሱ ግን የኮሚሽኑ ባለሥልጣናት አልጠቀሱም።-----ግብፅ ለሶማሊያ የጦር መሳሪያ ማስታጠቅ ጀመረች።መሳሪያ የጫኑ ሁለት የግብፅ የጦር አዉሮፕላኖች ትናንት ሞቃዲሾ ማረፋቸዉን ዲፕላቶች አስታዉቀዋል።ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋር ወደብ ለመኮናተር ከተስማማች ወዲሕ የሞቃዲሾና የካይሮ ፍቅር ፀጥንቷል...more11minPlay
August 27, 2024የነሐሴ 21 ቀን 2016 ዓ/ም የዓለም ዜናዓርስተ ዜና --የእስራኤል ልዩ ኃይል እጅግ በጣም ውስብስብ ባለው ልዩ ዘመቻ ደቡባዊ ጋዛ ውስጥ ከሚገኝ የሃማስ ዋሻ ውስጥ አንድ ታጋች ማስለቀቁን ዛሬ አስታወቀ። የ52 ዓመቱ ታጋች ከ10 ወራት በፊት ነበር በሃማስ ከደቡባዊ እስራኤል በሃማስ ታጣቂዎች ታግቶ የተወሰደው ።--በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን ሰሞኑን በተከታታይ በደረሰ የመሬት መንሸራተት አደጋ 23 ሰዎች ሞቱ። በአደጋዉ ከሞቱት ሰዎች በተጨማሪ 2700 ያክል ነዋሪዎች ከቤት ንብረታቸዉ ተፈናቅለዋል።--የሱዳን ፈኖ ደራሽ ኃይል በዳርፉር ግዛት በስደተኞች መጠለያ ጣቢያ ላይ በፈጸሙት የከባድ መሳሪያ ጥቃት በትንሹ 20 ሰዎች ተገደሉ።...more11minPlay
August 26, 2024DW Amharic ነሐሴ 20 ቀን 2016 የዓለም ዜናDW Amharic--በስለት ሦስት ሰዎች የተገደሉባትን ዞሊንገን የጀርመን ምዕራባዊ ከተማን ቻንስለር ኦላፍ ሾልዝ እና ታዋቂ የሃገሪቱ ፖለቲከኞች ለህዝብ አጋርነታቸዉን በማሳየት ከተማዋን ጎበኙ። IS የተባለዉ ጽንፈኛ ቡድን ሃላፊነት በወሰደበት በዚህ ጥቃት ሦስት ጀርመናዉያን ተገድለዋል፤ ስምንት ሰዎች ደግሞ ቆስለዋል። --በሰሜን ጎንደር ዞን ጠለምት ወረዳ በደረሰ ናዳ ህይወታቸው ካለፈ 10 ሰዎች መካከል እስካሁን የስድስቱን አስከሬን ማግኘት እንዳልተቻለ ተገለፀ። በሌላ በኩል በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፤ ደቡብ አሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ፤ በኦሞ ወንዝና በቱርካና ሀይቅ ሙላት በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ተፈናቀሉ።...more12minPlay
August 24, 2024DW Amharic የነሐሴ 18 ቀን 2016 የዓለም ዜናበእስራኤል የፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂን መንግሥት በሚደግፉ እና በሚቃወሙ ሁለት ቡድኖች መካከል በተፈጠረው ግጭት ሁለት ኤርትራውያን መገደላቸውን ፖሊስ አስታወቀ። በምዕራብ ጀርመን በምትገኘው ዞሊንገን ከተማ ሦስት ሰዎች ከተገደሉበት እና ሌሎች ስምንት ከቆሰሉበት ጥቃት ጋር ግንኙነት ሳይኖረው አይቀርም የተባለ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ሥር መዋሉን የሀገሪቱ ባለሥልጣናት አስታወቁ። የኤርትራ የቀድሞ የፋይናንስ ሚኒስትር ብርሃነ ኣብርሀ በእስር ላይ ሳሉ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። በጋዛ በትንሹ 50 ፍልስጤማውያን በእስራኤል ጥቃት መገደላቸውን የጋዛ የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።...more9minPlay
August 22, 2024የሐሙስ ነሀሴ 16 ቀን 2016 ዓ/ም የዓለም ዜናDW Amharic- ህወሃት የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደርን በአዳዲስ ተሿሚዎች ለመቀየር ውይይት እንደሚጀምር ማስታወቁ- ሶማሊያ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሀገሪቱ የሚያደርገውን በረራ እንደምታግድ መግለጿ- በአማራ ክልል ሁለት ዞኖች የመሬት መንሸራተት በሰብልና በመኖሪያ ቤቶች ላይ ጉዳት ማድረሱ- የኬንያ ፖሊስ ከ40 በላይ ሴቶችን በመግደል ከዕስር ያመለጠ አንድ ተጠርጣሪን ለጠቆመ የገንዘብ ወሮታ እንደሚከፍል ማስታወቁ-ታሊባን የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ መብቶች ልዩ ዘጋቢን ወደ አፍጋኒስታን እንዳይገቡ ማገዱ...more11minPlay
FAQs about የዓለም ዜና:How many episodes does የዓለም ዜና have?The podcast currently has 746 episodes available.