DW Amharic
--ዓመታዊዉ የዶቼ ቬለ የመገናኛ ብዙኀን መድረክ "መፍትሄዎችን መጋራት" በሚል መሪ ቃል ዛሬ ሰኔ 10 ቀን 2016 ዓ/ም ተጀመረ።በጀርመኗ ቦን ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው በዚህ መድረክ፤የዶቼ ቬለ ዋና ዳይሬክተር ፒተር ሊንቡርግ እና የጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚንስትር አናሊና ቤርቦክ በመድረኩ ንግግር አድርገዋል።
--የኢትዮጵያ ህዝብ አብዮታዊ ፓርቲ/ ኢሕአፓ/ ፕሬዝዳንት የሆኑትን፤ ፕሮፌሰር ዝናቡ አበራን ጨምሮ ዘጠኝ ሰዎች በገንዘብ ዋስትና ከእሥር እንዲለቀቁ ፍርድ ቤት ወሰነ።
--የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ የጦር ካቢኔ በመተናቸውን መበተናቸውን የእስራኤል ባለስልጣናት ገለፁ።