Sign up to save your podcastsEmail addressPasswordRegisterOrContinue with GoogleAlready have an account? Log in here.
በሣምንታዊው የከኤኮኖሚው ዓለም መሰናዶ የኢትዮጵያ፣ አፍሪካ እና ዓለምን ምጣኔ ሐብታዊ ይዞታ የተመለከቱ ትንታኔዎች፣ ቃለ መጠይቆች እና ዘገባዎች ይቀርባሉ። ይኸ መሰናዶ ሀገራት የሚያወጧቸውን ኤኮኖሚያዊ ፖሊሲዎች፣ መሪዎች የሚወስዷቸውን ምጣኔ ሐብታዊ ውሳኔዎች በመፈተሽ ጥቅም እና ጉዳታቸውን ያቀርባል።... more
FAQs about ከኤኮኖሚው ዓለም:How many episodes does ከኤኮኖሚው ዓለም have?The podcast currently has 100 episodes available.
January 24, 2024ኢትዮጵያ ለካፒታል ገበያ አገልግሎት አቅራቢዎች ፈቃድ መስጠት ልትጀምር ነውኢትዮጵያ በተያዘው ዓመት ሥራ ይጀምራል ተብሎ በሚጠበቀው የካፒታል ገበያ አገልግሎት ለሚያቀርቡ ድርጅቶች ፈቃድ ለመስጠት የምታደርገውን ዝግጅት እያጠናቀቀች ነው። የኢትዮጵያ ሴኪዩሪቲስ ኤክስቼንጅ ሥራ ለመጀመር የኢንቨስትመንት ባንኮችን ጨምሮ አስራ አምስት ዓይነት የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪዎች ይፈልጋል። እንደ ዋትስአፕ እና ቴሌግራም በመሳሰሉ መንገዶች የአክሲዮን ድርሻዎች በማሻሻጥ ሥራ ላይ የተሰማሩ ግለሰቦች እና ድርጅቶች ከኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን አዲስ ፈቃድ መውሰድ አለባቸው።...more10minPlay
January 17, 2024የአውሮፓ ኅብረት የደን ጭፍጨፋ መከላከያ ሕግ የኢትዮጵያ ቡና ገበሬዎች እና ላኪዎችን አስግቷልየአውሮፓ ኅብረት ደን ተጨፍጭፎ የሚመረቱ ሸቀጦች ወደ ገበያው እንዳይገቡ ለመከልከል ያወጣው ሕግ የኢትዮጵያ ቡና አምራች ገበሬዎች ማኅበራት እና ላኪዎችን አስግቷል። ባለፈው ሰኔ የጸደቀው ሕግ ከኢትዮጵያ ቡና የሚገዙ የአውሮፓ ኩባንያዎችን ገና ካሁኑ እያሸሸ ነው። ከምታመርተው ቡና 30 በመቶውን ወደ አውሮፓ የምትልከው ኢትዮጵያ በሕጉ የተቀመጠውን ቅድመ ሁኔታ ካላሟላች ትልቅ ገበያ ልታጣ ትችላለች።...more11minPlay
January 09, 2024የጀርመን ገበሬዎች የአንድ ሣምንት ተቃውሞ ለምን ተቀሰቀሰ?የጀርመን መንግሥት ለግብርና ሥራዎች ይሰጥ የነበረውን ድጎማ በመቃወም የሀገሪቱ ገበሬዎች ለአንድ ሣምንት የሚዘልቅ ተቃውሞ ጀምረዋል። ተቃውሞው ባለፈው ሰኞ ሲጀመር በርሊንን ጨምሮ በብዙ ከተሞች መንገዶች እና አውራ ጎዳናዎች በትራክተሮች ተዘግተው ነበር። የጀርመን ገበሬዎች ለግብርና ሥራ ናፍጣ ሲሸምቱ ለሚከፍሉት ታክስ ከመንግሥት ማካካሻ ይሰጣቸዋል።...more10minPlay
January 03, 2024በኢትዮጵያ እና ሶማሌላንድ ሥምምነት የተቀየመችው ሶማሊያ ፊቷን ወደ ግብጽ አዙራለችኢትዮጵያ ከሶማሌላንድ በተፈራረመችው “የአጋርነት እና የትብብር የመግባቢያ ሥምምነት” የተቆጣችው ሶማሊያ ፊቷን ወደ ግብጽና ቃጣር አዙራለች። ሶማሌላንድ ኢትዮጵያ እውቅና የምትሰጥ የመጀመሪያ ሀገር በመሆኗ አመስግና ሥምምነቱን “የሚያስተጓጉሉ ወይም የሚቃወሙ” ወገኖችን አስጠንቅቃለች። ተንታኞች የለየለት ጦርነትም ባይሆን የእጅ አዙር ግጭትን ይሰጋሉ...more10minPlay
December 27, 2023ዕዳ መክፈል ከተሳናቸው ሀገራት ጎራ የተመደበችው ኢትዮጵያ ከቦንድ ባለቤቶች እየተደራደረች ነውመቀመጫውን በኒው ዮርክ ያደረገው ፊች ሬቲንግስ ኢትዮጵያ 33 ሚሊዮን ዶላር ወለድ ሳትከፍል መቅረቷ ከተረጋገጠ በኋላ በዓለም ገበያ የተሸጠውን ቦንድ ምድባ ወደ ያልተከፈለ ዝቅ አድርጎታል። መንግሥት እና የኢትዮጵያ ቦንድ ባለቤቶች በወለድ እና ዕዳ አከፋፈል ላይ እየተደራደሩ ነው። የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ሁሉም አበዳሪዎች እኩል መስተናገድ አለባቸው በሚል አቋማቸው እንደጸኑ ነው። ኢትዮጵያ ከግል አበዳሪዎች ቦንድ ሸጣ የተበደረችው አንድ ቢሊዮን ዶላር ከአጠቃላይ የውጭ ዕዳ ያለው ድርሻ ሁለት በመቶ ገደማ ነው።...more11minPlay
December 20, 2023ሶማሊያ 4.5 ቢሊዮን ዶላር ዕዳ ሲሰረዝላት ዜጎቿ የደቀቀው ኤኮኖሚ ያንሰራራል የሚል ተስፋ ሰንቀዋልባለፈው ሣምንት ከፍተኛ መጠን ያለው ዕዳ የተሰረዘላት ሶማሊያ ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት 100 ሚሊዮን ዶላር የተራዘመ የብድር አቅርቦት ጸድቆላታል። የሶማሊያ 4.5 ቢሊዮን ዶላር ዕዳ ከተሰረዘ በኋላ ዜጎቿ ኤኮኖሚው ያንሰራራል የሚል ተስፋ ሰንቀዋል። በዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት እና የዓለም ባንክ የጸደቀው የዕዳ ስረዛ የሶማሊያን የውጭ ብድር ከ5.3 ቢሊዮን ዶላር ወደ 700 ሚሊዮን ዶላር ቀንሶታል። ውሳኔውን የሰሙ የሶማሊያ ዜጎች ባረጀው ምትክ የመገበያያ ገንዘብ እንዲታተም ይሻሉ።...more10minPlay
December 13, 2023የኢትዮጵያ ቦንድ ባለቤቶች እና የገንዘብ ሚኒስቴር ባለሥልጣናት ሐሙስ አንገብጋቢ ውይይት አላቸውየኢትዮጵያ መንግሥት ኃይለማርያም ደሳለኝ ሥልጣን ላይ ሳሉ የተሸጠው ቦንድ ወለድ ከ6.625 ወደ 5.5 በመቶ ዝቅ እንዲል ይፈልጋል። ከዚህ በተጨማሪ በሚቀጥለው ዓመት የሚጎመራው ቦንድ የሚከፈልበት ጊዜ እንዲሸጋሸግ ይሻል። የኢትዮጵያ ቦንድ ባለቤቶች እና የገንዘብ ሚኒስቴር ባለሥልጣናት ነገ ለመነጋገር ቀጠሮ አላቸው። ቀጠሮው ኢትዮጵያ 33 ሚሊዮን ዶላር ወለድ እንደማትከፍል ካሳወቀች በኋላ የተያዘ ነው።...more11minPlay
December 06, 2023የኢትዮጵያ የዕዳ ክፍያ እፎይታ ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት ጋር በሚኖራት ሥምምነት እጣ ፈንታ ላይ የተንጠለጠለ ነውየዋጋ ንረት እና የውጭ ምንዛሪ እጥረት የበረታባት ኢትዮጵያ ከአበዳሪዎቿ የሁለት ዓመት የዕዳ ክፍያ እፎይታ አግኝታለች። ሥምምነቱ ለኢትዮጵያ 1.5 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያድን የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምኅረቱ ተናግረዋል። ሀገሪቱ ባለፈው ዓመት ለነዳጅ መግዣ ብቻ ያወጣችው 4 .1 ቢሊዮን ዶላር ከዕቃዎች የወጪ ንግድ ካገኘችው የበለጠ ነው...more10minPlay
November 29, 2023ኢትዮጵያ ሊቲየምን ጨምሮ በአምስት ዘርፎች የጀርመን ኩባንያዎችን መዋዕለ-ንዋይ ትፈልጋለችበኢትዮጵያ ሐይድሮጅን ማምረት ለሚሹ ኩባንያዎች መንግሥት ከታላቁ የኅዳሴ ግድብ 500 ሜጋዋት ኃይል እንደሚመድብ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ኢዮብ ተካልኝ ተናግረዋል። መንግሥታቸው ሊቲየምን ጨምሮ በአምስት የተመረጡ ዘርፎች ጀርመኖች በኢትዮጵያ ኢንቨስት እንዲያደርጉ ጋብዟል። የጀርመን ባለወረቶች እንደሚሉት ግን የውጭ ምንዛሪ እጥረት ፈተና ነው።...more11minPlay
FAQs about ከኤኮኖሚው ዓለም:How many episodes does ከኤኮኖሚው ዓለም have?The podcast currently has 100 episodes available.