Sign up to save your podcastsEmail addressPasswordRegisterOrContinue with GoogleAlready have an account? Log in here.
በሣምንታዊው የከኤኮኖሚው ዓለም መሰናዶ የኢትዮጵያ፣ አፍሪካ እና ዓለምን ምጣኔ ሐብታዊ ይዞታ የተመለከቱ ትንታኔዎች፣ ቃለ መጠይቆች እና ዘገባዎች ይቀርባሉ። ይኸ መሰናዶ ሀገራት የሚያወጧቸውን ኤኮኖሚያዊ ፖሊሲዎች፣ መሪዎች የሚወስዷቸውን ምጣኔ ሐብታዊ ውሳኔዎች በመፈተሽ ጥቅም እና ጉዳታቸውን ያቀርባል።... more
FAQs about ከኤኮኖሚው ዓለም:How many episodes does ከኤኮኖሚው ዓለም have?The podcast currently has 117 episodes available.
June 19, 2024ለብድር አሰጣጥ ጠበቅ ያሉ መመሪያዎች ያወጣው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እስከ ዛሬ የት ነበር?የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የመንግሥት ባንኮች እና የመንግሥት የልማት ድርጅቶች እንደ “ተዛማጅ ወገኖች” እንደሚቆጠሩ ወስኗል። የባንኩ መመሪያ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለተቋማቱ የሚሰጠውን የብድር መጠን እንዲገድብ የሚያስገድድ ነው። እስከ ጎርጎሮሳዊው 2022/23 ብቻ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች 777.8 ቢሊዮን ብር የንግድ ባንክ ዕዳ አለባቸው።...more10minPlay
June 12, 2024የኢትዮጵያ የበጀት ጉድለት በ2017 ከአጠቃላይ ሀገራዊ የምርት መጠን 2.1% ድርሻ ይኖረዋልበ2017 የኢትዮጵያ የበጀት ጉድለት ከአጠቃላይ ሀገራዊ የምርት መጠን 2.1% ድርሻ እንደሚኖረው አቶ አሕመድ ሽዴ ተናግረዋል። መንግሥት ለሚቀጥለው ዓመት ያዘጋጀው 971 ቢሊዮን ብር በጀት 358.5 ቢሊዮን ብር ጉድለት ይገጥመዋል። ከ2017 በጀት 139.3 ቢሊዮን ብር ለዕዳ ክፍያ የታቀደ ነው። መንግሥት ኤኮኖሚው በ8.4% ያድጋል ብሎ ይጠብቃል። ኢትዮጵያ የምትከተለው የውጭ ምንዛሪ ግብይት ሥርዓት በ2017 እንደሚቀጥል የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሽዴ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ገልጸዋል።...more11minPlay
June 05, 2024ደቡብ ኮሪያ እና አፍሪካ አንዳቸው ከሌላው የሚፈልጉት ምንድነው?በመጀመሪያው የኮሪያ አፍሪካ ጉባኤ የኢትዮጵያ፣ የኤርትራ እና የኬንያን ጨምሮ 25 የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች ተገኝተዋል። ከደቡብ ኮሪያ የወጪ እና ገቢ ንግድ አፍሪካ ያላት ድርሻ ከ2% ያነሰ ነው። የአፍሪካ መሪዎች ደቡብ ኮሪያ ከደረሰችበት የቴክኖሎጂ ዕድገት እንድታቋድሳቸው ይፈልጋሉ። ደቡብ ኮሪያ በአንጻሩ በአፍሪካ ማዕድናት ላይ አይኗን ጥላለች።...more9minPlay
May 29, 2024የኢትዮጵያ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ብድር 65 ቢሊዮን ዶላር ደርሷልየኢትዮጵያ አጠቃላይ ብድር 65 ቢሊዮን ዶላር መድረሱን የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሽዴ ባለፈው ሣምንት ተናግረዋል። ወደ 1.2 ትሪሊዮን ብር ያሻቀበው የመንግሥት የሀገር ውስጥ ብድር “ጫናው፣ ክምችቱ እየጨመረ፣ እየከፋ” ሊሔድ እንደሚችል በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አብርሃም ዓለማየሁ አስጠንቅቀዋል። ሀገሪቱ በጦርነት የወደመውን መልሶ ለመገንባት የጀመረችው ጥረትም በታቀደው ፍጥነት ተግባራዊ አልሆነም።...more10minPlay
May 22, 2024አዲሱ የገጠር መሬት አስተዳደር እና አጠቃቀም አዋጅ ምን ይዞ መጣ?የኢትዮጵያ ገበሬዎች እና አርብቶ አደሮች በመሬታቸው የመጠቀም መብታቸውን አስይዘው ከባንክ እንዲበደሩ የሚፈቅድ አዋጅ ባለፈው ሣምንት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጸድቋል። በአዲሱ የገጠር መሬት አስተዳደር እና አጠቃቀም አዋጅ ባለመብቶች መሬታቸውን ማከራየት እና ከባለ ሐብቶች ጋር በጋራ ማልማት ጭምር ተፈቅዶላቸዋል።...more12minPlay
May 15, 2024የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር የወሰደው እርምጃ ለውጥ እያመጣ ነው?የኢትዮጵያ ስታስቲክስ አገልግሎት እንደሚለው በሚያዝያ ወር አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት የሚያድግበት ፍጥነት የመለዘብ አዝማሚያ አሳይቶ 23 በመቶ ገደማ ደርሷል። የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምኅረቱ የታየውን ለውጥ “ታላቅ ዕምርታ” ብለውታል። የምግብ ነክ ዕቃዎች የዋጋ ግሽበት ግን ባለፈው ሚያዝያ ወር 27 በመቶ ሆኖ ተመዝግቧል። ዳቦ እና ጥራጥሬን የመሳሰሉ ምግቦች ከ2015 ሚያዝያ አኳያ አሁንም ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ አሳይተዋል።...more10minPlay
May 08, 2024በጋዛ የወደመውን መልሶ ለመገንባት እስከ 50 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋልእስራኤል በጋዛ ለሰባት ወራት ባካሔደችው ወታደራዊ ዘመቻ የወደመውን መልሶ ለመገንባት እስከ 50 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ የተመድ አስታውቋል። ጦርነቱ ከ1.7 ሚሊዮን በላይ ሰዎችን ወደ ድሕነት ሲገፋ ሥራ አጥነት ከ25% ወደ 46 አሻቅቧል። በጦርነቱ የወደሙ መኖሪያ ቤቶችን መልሶ ለመገንባት እስከ 80 ዓመታት ሊወስድ ይችላል።...more9minPlay
May 01, 2024ሶማሌላንድ የበርበራ ወደብ የኢትዮጵያን 30 በመቶ ጭነት እንዲያስተናግድ ትፈልጋለችየተባበሩት ዓረብ ኤሚሬቶች ንብረት የሆነው ዱባይ ወርልድ ኩባንያ የሚያስተዳድረው የበርበራ ወደብ የኢትዮጵያን 30 በመቶ ጭነት እንዲያስተናግድ የሶማሌላንድ ባለሥልጣናት አቅደዋል። ለዚህም የወደብ አጠቃቀም እና የጉምሩክ ሥርዓቶችን የተመለከተ ሥምምነት በኢትዮጵያ እና በሶማሌላንድ መካከል መፈረም አለበት። ሥምምቱ በሚቀጥሉት 60 ቀናት ሊፈረም እንደሚችል የሶማሌላንድ የወደቦች አስተዳደር ባለሥልጣን ኃላፊ ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል።...more10minPlay
April 17, 2024የኢትዮጵያ ገበያ ለውጭ ባለወረቶች ሲፈቀድ ባለሙያዎች ተስፋ እና ሥጋት ተሰምቷቸዋልለኢትዮጵያውያን ተከልለው የቆዩ የወጪ እና ገቢ ንግድ ሥራዎች ለውጭ ባለወረቶች ተፈቅደዋል። የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ቦርድ መመሪያ የውጭ ባለወረቶች በጅምላ እና ችርቻሮ ንግድ ዘርፎች ጭምር እንዲሳተፉ የፈቀደ ነው። መንግሥት ለረዥም ዓመታት ሲከተል በቆየው ፖሊሲ ረገድ ያደርገው ለውጥ ለአንዳንድ ባለሙያዎች ተስፋ ለሌሎች ሥጋት ያጫረ ሆኗል።...more11minPlay
April 10, 2024የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ የኢንቨስተሮችን የድርሻ ድልድል እያካሔደ ነውከ48 ኢንቨስተሮች 1.5 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያሰባሰበው የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ የድርሻ ድልድል እያካሔደ ነው። በዚህ ሣምንት የሚጠናቀቀው ድልድል ባለድርሻዎች ምን ዓይነት መብት እንደሚኖራቸው ይወስናል። የናይጄሪያ ኤክስቼንጅ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚው የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ የቦርድ አባል እንደሚሆኑ አስታውቋል።የኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ሥራ ሲጀምር ግብይቱ የሚመራበትን ሕገ-ደንብ ለሕዝብ ይፋ አድርጓል። ከዚህ በተጨማሪ ግብይት የሚካሔድበትን ቴክኖሎጂ ለመዘርጋት አቅራቢዎች የሚመርጥበት ደረጃ ላይ ነው።...more10minPlay
FAQs about ከኤኮኖሚው ዓለም:How many episodes does ከኤኮኖሚው ዓለም have?The podcast currently has 117 episodes available.