Sign up to save your podcastsEmail addressPasswordRegisterOrContinue with GoogleAlready have an account? Log in here.
ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና ዜናዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ። የዶይቼ ቬለን ዜናዎች በአፕል ፖድካስት... more
FAQs about የዓለም ዜና:How many episodes does የዓለም ዜና have?The podcast currently has 679 episodes available.
June 28, 2025DW Amharic የሰኔ 21 ቀን 2017 የዓለም ዜናበደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን ታጣቂዎች ሁለት አርሶ አደሮችን በጥይት ደብድበው መግደላቸውን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ። ኢትዮጵያን ጨምሮ በ39 ኢኮኖሚዎች ግጭት እና አለመረጋጋት ከየትኛውም የዓለም ክፍል በባሰ ሁኔታ ድሕነት እና አስከፊ ረሐብ ማባባሱን ዓለም ባንክ ይፋ አደረገ። አዲስ የተሾሙት የሱዳን መከላከያ ሚኒስትር እና የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ቃለ መሐላ ፈጸሙ። የኑክሌር ሳይንቲስቶች እና ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖችን ጨምሮ ኢራን ከእስራኤል ባደረገችው ውጊያ የተገደሉ 60 ሰዎች ብሔራዊ ሥርዓተ ቀብር ተፈጸመ። በጋዛ ሠርጥ በተፈጸሙ የእስራኤል ጥቃቶች ቢያንስ 81 ተገደሉ...more12minPlay
June 27, 2025የሰኔ 20 ቀን 2017 ዓ.ም.የዓለም ዜናየሰኔ 20 ቀን 2017 ዓ.ም. አርዕስተ ዜናከመላ ኢትዮጵያ፣ በሕገወጥ መንገድ በመተማ ዮሐንስ በኩል፣ ወደ ሱዳን የሚሰደዱ ወጣቶችና ህፃናት ቁጥር በእጅጉ እየጨመረ መሆኑን የምዕራብ ጎንደር ዞን አስታወቀ። በዞኑ የሴቶች፣ ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ እንዳለውበተለይ ከትግራይ ክልል የሚሰደዱት ቁጥር ከፈተኛ ነው።ምያንማር ውስጥ አሁንም በአጋቾች እንደተያዙ ነው የተባሉ 42 ኢትዮጵያውን እጣ ፈንታ አለመታወቁን በምያንማር የተጎጂ ወጣቶች ቤተሰቦች አስተባባሪ ለዶቼቬለ ተናገሩ። ዋሽንግተን ያሸማገለቻቸው የኮንጎ ዴሞክራሲያዊት ሪፐብሊክና ሩዋንዳ ዛሬ ዋሽንግተን ውስጥ የሰላም ስምምነት ይፈራረማሉ ተብሎ እየተጠበቀ ነው።...more11minPlay
June 26, 2025የሰኔ 19 ቀን 2017 የዓለም ዜና-የኢትዮጵያ መንግስት የሥራ ሁኔታ እንዲሻሻልላቸዉ የጠየቁ የሕክምና ባለሙያዎችን ማሠርና ማዋካቡን እንዲያቆም ሑዩማን ራይትስ ዋች ጠየቀ።ዓለም አቀፉ የሠብአዊ መብት ተሟጋች እንድርጅት እንደሚለዉ የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ለጥያቄዉ ተገቢ መልስ ከመስጠት ይልቅ ጠያቂዎቹን ያስራሉ፣ያዋክባሉ፣ ማሕበራቸዉን ያግዳሉም።---የኬንያ ፀጥታ አስከባሪዎች ትናንት አደባባይ በወጡ ተቃዉሞ ሰልፈኞች ላይ በወሰዱት የኃይል ርምጃ የሞቱት ሰዎች ቁጥር 16 ደረሰ።ከ400 በላይ ቆስለዋል።--የእስራኤል-የዩናይትድ ስቴትስ ባለሥልጣናትና የኢራን ጠላቶቻቸዉ የገጠሙት የቃላት ዉዝግብ እንቀጠለ ነዉ።ሶሥቱም በየፊናቸዉ ድል እድርገናል ይላሉ።...more11minPlay
June 25, 2025የረቡዕ ሰኔ 18 ቀን፣ 2017 ዓ.ም የዓለም ዜናድሬዳዋ፥ በኢትዮጵያ ምሥራቃዊ አካባቢዎች ብርቱ ዝናብ ይጠበቃል፤ ጄኔቫ፦ ኤርትራ ተመድ የመብት ጥሰት ጥርጣሬ ላይ የሚያደርገው ምርመራ እንዲቋረጥ መሻቷ ተገለጠ፤ ኖዋክቾት፥ ዩክሬን ሩስያን ለመገዳደር አፍሪቃ ውስጥ ተጨማሪ ኤምባሲ መክፈቷ ተገለጠ፤ ናይሮቢ፥ በኬንያ የአደባባይ ተቃውሞ ቢያንስ ሁለት ተገደሉ፤ ዘ ሔግ፥ የኢራን እና እሥራኤል የተኩስ አቁም ስምምነት በቀላሉ የመጣስ ሥጋት ያጠላበት ነው፤ ዘ ሔግ፦ ዩናይትድ ስቴትስ ለኔቶ መከላከያ ቄቁርጠኛ አቋም አላት ተባለ...more9minPlay
June 24, 2025የዓለም ዜና፤ ሰኔ 17 ቀን፣ 2017 ማክሰኞ--ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እስራኤልና ኢራን የተኩስ አቁም ስምምነቱን ጥሰዋል ሲሉ ወቀሱ። በሌላ በኩል ኢራን የኒኩሊየር ተቋሞችዋን ለማደስ ቅድመ ዝግጅት ላይ መሆንዋን አስታዉቃለች።--የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት የ(ኔቶ) መሪዎች ኔዘርላንድስ ላይ ታሪካዊ የተባለዉን የሁለት ቀናት ጉባኤ ጀመሩ። 32 የዓለም ሃገራት አባላት የሆኑበት የዓለም ትልቁ የደህንነት ድርጅት ለደህንነት ተጨማሪ ወጭ ለማዉጣት ይስማማሉ አልያም ያለስምምነት ይበተናሉ ተብሎ ይጠበቃል።--በዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡኔ ገብረመንፈስ ቅዱስ ገዳም በሚኖሩ መነኮሳት ላይ በተፈጸመ ጥቃት የአንድ መናኝ ህይወት ጠፋ፤ አንድ አባት ጉዳት ደርሰባቸዉ።...more14minPlay
June 23, 2025የሰኔ 16 ቀን 2017 ዓ.ም. የዓለም ዜናኢራን ትናንት እሑድ በአሜሪካ ለደረሰባት ጥቃት አጸፋዋ የከፋ ሊሆን እንደሚችል ዛተች። አሜሪካ ኢራን ላይ ያደረሰችውን ጥቃት ተከትሎ የኢራን እስራኤል ፍጥጫ በዲፕሎማሲ መፍትሄ እንዲያገኝ የተለያዩ ሃገራት ጥሪ አቀረቡ። ቴህራን በበኩሏ በዩናይትድ ስቴትስ የተፈጸመባት ጥቃት የዲፕሎማሲ እና ውይይት መርሆዎችን መካድ ነው ብላለች። የሶማሊያ ጦር ኃይላት በትናንትናው ዕለት በሀገሪቱ ማዕከላዊ አካባቢዎች ቢያንስ 20 የሚሆኑ የአሸባብ ተዋጊዎችን ገደሉ። በርካቶችንም አቆሰሉ። የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል መሪ ሌተናል ጀነራል መሀመድ ሀምዳን ዳጋሎ ቡድናቸው ከግብጽ ጋር ያለውን ያለመግባባት በውይይት ለመፍታት እንደሚፈልግ አስታወቁ።...more12minPlay
June 21, 2025የሰኔ 14 ቀን 2017 ዓ.ም የዓለም ዜናበናይጄሪያ አንዲት ሴት አጥፍቶ ጠፊ በፈጸመችው የቦምብ ጥቃት 20 የጸረ እስላማዊ ጀሃድ ታጣቂዎች መገደላቸውን ተሰማ።እስራኤል ኢስፋሃን የሚገኘውን የኢራን የኒኩሌር ማብለያ ተቋም ላይ ጥቃት መፈጸሟን የኢራን መገናኛ ብዙሃን ዘገቡ። እስራኤል በተቋሙ ጥቃት ብትፈፅምም ምንም አይነት ሰዎችን ሊጎዳ የሚችል ኬሚካል አለመፍሰሱን አክለዋል። የሩስያው ፕረዚደንት ቭላድሚር ፑቲን ኢራን የኒኩሌር የጦር መሳሪያ ስለማምረቷ ምንም አይነት ተጨባጭ ማስረጃ እንደሌለ ለእስራኤል ደጋግመን ነግረናታል አሉ።...more11minPlay
June 20, 2025የሰኔ 13 ቀን 2017 የዓለም ዜና-የኢጣሊያና የአዉሮጳ ሕብረት መሪዎች የአፍሪቃ ሥደተኞችን ለመግታት ለተለያዩ የአፍሪቃ ሐገራት ሊሰጥ ሥለታቀደዉ ርዳታ ዛሬ ተነጋገሩ።---የሥደተኞችን ቁጥር ለመቀነስ የአዉሮጳ ሕብረት ኢትዮጵያን ጨምሮ ለ14 የአፍሪቃ ሐገራት 5.5 ቢሊዮን ዩሮ ይሰጣል።---የእስራኤልና የኢራን የጦር ሜዳ ዉጊያ የዲፕሎማሲ እንኪያ ሰላንቲያም ዛሬም እንደመሰንበቻዉ ቀጥሎ ዉሏል።የእስራኤል ጦር የኢራን የሚሳዬል ማወንጨፊያዎችን ጨምሮ የተለያዩ ተቋማትን መደብደቡን አስታዉቋል።የኢራን ሚሳዬሎችም ዛሬ በእስራኤል ግዛቶች ላይ ሲዝንቡ ነዉ የዋሉት።-በዲፕሎማሲዉ መስክ የኢራንና የሶስት የአዉሮጳ ሐገራት ዉጪ ጉዳይ ሚንስትሮች እየተነጋገሩ ነዉ።...more12minPlay
June 19, 2025የሰኔ 12 ቀን 2017 ዓ.ም. የዓለም ዜና*በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ወለጋ ዞን 17 ንጹሀን ዜጎች በታጣቂዎች ተገደሉ*ፍርድ ቤት የቀድሞው የሀዋሳ ከተማ ከንቲባን በነጻ አሰናበተ*ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና ሩዋንዳ የሰላም ስምምነት ሊፈራረሙ ነው*እስራኤል በኢራን ላይ የአፀፋ ርምጃ እንደምትወስድ አሳሰበች*ዜጎችን ከእስራኤል እና ኢራን የማስወጣት ርምጃው ቀጥሏል*ሩሲያ ጀርመንን አስጠነቀቀች...more11minPlay
FAQs about የዓለም ዜና:How many episodes does የዓለም ዜና have?The podcast currently has 679 episodes available.