Sign up to save your podcastsEmail addressPasswordRegisterOrContinue with GoogleAlready have an account? Log in here.
ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና ዜናዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ። የዶይቼ ቬለን ዜናዎች በአፕል ፖድካስት... more
FAQs about የዓለም ዜና:How many episodes does የዓለም ዜና have?The podcast currently has 747 episodes available.
September 30, 2024የመስከረም 20 ቀን 2017 የዓለም ዜናየተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች በኻርቱም የሚገኝ የአምባሳደሯ መኖሪያ ቤት በወታደራዊ አውሮፕላን ተደብድቧል በሚል ያቀረበችውን ክስ የሱዳን ጦር አስተባበለ። በደቡብ አፍሪካ ምሥራቅ ኬፕ ክፍለ ግዛት በተፈጸመ ጥቃት የተገደሉ ሰዎች ቁጥር ወደ 18 አሻቀበ። ርዋንዳ ኃይለኛ ተላላፊ በሆነው ኢቦላ መሰል የማርበርግ ቫይረስ ወረርሽኝ ስምንት ሰዎች መሞታቸውን አስታወቀች። እስራኤል ሊባኖስን በእግረኛ ወታደሮች ከወረረች ሒዝቦላሕ ለውጊያ ዝግጁ መሆኑን አስታወቀ። የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር ዮቭ ጋላንት ሀገራቸው እግረኛ ወታደሮቿን ወደ ሊባኖስ ልታዘምት እንደምትችል ፍንጭ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ ኢራንን አስጠንቅቀዋል...more11minPlay
September 28, 2024የመስከረም 18 ቀን 2017 የዓለም ዜናጠቅላይ ሚኒስትር ሐምዛ አብዲ ባሬ ኢትዮጵያ ከሶማሌላንድ የተፈራረመችው የመግባቢያ ሥምምነት የሶማሊያን የግዛት አንድነት ይጥሳል ሲሉ ከሰሱ። የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ታዬ አጽቀ ሥላሴ የሀገራቸው “ዓላማ በቀጠናው የጋራ ዕድገት እና ብልጽግና መፍጠር” እንደሆነ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ እና የአይኤምኤፍ ባለሙያዎች በተራዘመ የብድር አቅርቦት የመጀመሪያ ግምገማ ተስማሙ። የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል በዳርፉር ግዛት በምትገኘው አል-ፋሽር ለሁለት ቀናት በፈጸመው ጥቃት 48 ሰዎች ተገደሉ። የሊባኖሱ ሒዝቦላሕ መሪው ሐሳን ናስረላሕ እስራኤል በፈጸመችው የአየር ጥቃት መገደላቸውን አረጋገጠ።...more11minPlay
September 26, 2024የመስከረም 16 ቀን 2017 ዓ/ም የዓለም ዜናDW Amharic-የዛሬው የዓለም ዜና በኢትዮጵያ የጋዜጠኞች እና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እስር እና ወከባ እየጨመረ መጥቷል መባሉ፤በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያን የመስቀል ደመራ በዓል በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ መከበሩ፤የሱዳን ጦር በዋና ከተማይቱ ካርቱም የመድፍ እና የአየር ድብደባ መጀመሩ ፤ደቡብ አፍሪቃ በፀረ አፓርታይድ ትግሉ ወቅት በስደት ሆነው ህይወታቸውን ያጡ ዜጎቿን አስከሬን ወደ ሀገር መመለሷ፤የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ የተኩስ አቁም ስምምነት ሀሳብን ውድቅ ማድረጋቸው እና ሩሲያ የምዕራቡን ዓለም ለመገዳደር አዲስ የኒዩክሌር ጦር መሳሪያ አጠቃቀም ሰነድ ማውጣቷን ያስቃኛል።...more11minPlay
September 25, 2024የመስከረም 15፣2017 የዓለም ዜናደቡብ ኢትዮጵያና ጋምቤላ ክልሎች በደረሱ የመኪና አደጋዎች 35 ሰዎች ሞቱ።ናይሮቢ-የኬንያ እናቶች ጥሪ፣ የአምንስቲ ጥያቄ።አቡጃ-በኢትዮጵያ በኩል ያለፈ አደንዛዥ ዕፅ ሌጎስ ላይ ተያዘ።ቫቲካን-የእስራኤል-ሒዝቡላሕ ዉጊያና የርዕሠ ጳጳሱ ተማፅዕኖ።ኒዮርክ-የዓለም መሪዎች ጥሪና የእስራኤል ሊባኖስ ዉጊያ...more12minPlay
September 23, 2024የዓለም ዜና፤ መስከረም 13 ቀን 2017 ዓ.ም ሰኞ--ሶማሊያ ከግብፅ ከፍተኛ መጠን ያለዉ የጦር መሳሪያን ለሁለተኛ ጊዜ ተረከበች። ግብፅ ዜጎችዋ በቶሎ ከሶማሌላንድ እንዲወጡም ጠይቃለች።--ፓኪስታን ዉስጥ የኢትዮጵያንና የሩስያ ዲፕሎማቶችን ጨምሮ የተለያዩ ሃገራት ልዑኮች ከጥቃት መትረፋቸዉ ተመለከተ።--ሱዳን ባለፈው ነሐሴ ወር ብቻ በኮሌራ የሞቱት ሰዎች ቁጥር ወደ 388 ከፍ ማለቱ ተነገረ። በወረርሽኙ ወደ 13,000 ሰዎች ተይዘዋል።--እስራኤል በሊባኖስ እያካሄደች ያለዉ ጥቃት 'አደገኛ መዘዝ' ያስከትላል ስትል ኢራን አስጠነቀቀች። በእስራኤል እና በሂዝቦላ ሚሊሻ መካከል እየጠነከረ የመጣው ዉጥረት ፤ በመካከለኛው ምስራቅ የሚታየዉን ቀዉስ እንዳያሰፋ ስጋት አሳድሯል።...more12minPlay
FAQs about የዓለም ዜና:How many episodes does የዓለም ዜና have?The podcast currently has 747 episodes available.