Sign up to save your podcastsEmail addressPasswordRegisterOrContinue with GoogleAlready have an account? Log in here.
በዐበይት የኢትዮጵያ፣ የአፍሪካ፣ የአውሮፓ እና የዓለም ጉዳዮች ላይ ዜናዎች፣ ቃለ-መጠይቆች እና ጥልቅ ትንታኔዎች ይቀርባሉ። በዐበይት የኢትዮጵያ፣ የአፍሪካ፣ የአውሮፓ እና የዓለም ጉዳዮች ላይ ዜናዎች፣ ቃለ-መጠይቆች እና ጥልቅ ትንታኔዎች ይቀርባሉ። ኢትዮጵያን ጨምሮ በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚገኙ የዶይቼ... more
FAQs about ዜና መጽሔት:How many episodes does ዜና መጽሔት have?The podcast currently has 1,996 episodes available.
January 26, 2024"ለሶማሌላንድ ዕውቅና መስጠት የስምምነቱ አካል ነው" በኢትዮጵያ የሶማሌላንድ ተወካይእአምባሳደር አብዱላሂ ሶማሊያን የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የቀጣናው አለመረጋጋት ምንጭ አድርገው ከሰዋል።«በአንጻሩ ሶማሊላንድ ለቀጣናው መረጋጋት ጉልህ ድርሻ አላት። "ኢትዮጵያም፣ ድንበሯም እንዲከበር እንጠብቃለን። ሁለተኛ ፣ ሶማሊላንድ በሕግ የፀና እውቅና ያለው ግዛት ሆኖ መታወቅ አለበት። ሶማሊላንድ አልሸባብን እና ሽብርተኝነት ትዋጋለች"ብለዋል።...more4minPlay
January 24, 2024የረቡዕ ጥር 15 ቀን፣ 2016 ዓ.ም ዜና መጽሄትጉጂ ዞን 12 ሰዎች በታጣቂዎች ተገድለዋል፤ አሶሳ ሆስፒታል የመድኃኒትና የአቅርቦት እጥረት ገጥሞታል፤ መቐለ በሺህዎች የሚቆጠሩ የተቃውሞ ሰልፍ አድርገዋል፤ የምግብ እጥረት በአበርገሌና በፃግበጂ ወረዳዎች ሥጋት ፈጥሯል ። ዝርዝሩን ከድምፁ ያድምጡ ።...more18minPlay
January 24, 2024የምግብ እጥረት በአበርገሌና በፃግበጂ ወረዳዎችበአማራ ክልል ዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር በአካባቢው ታጣቂዎችና በመንግሥት ኃይሎች መካከል በነበረ ጦርነት ተፈናቅለው የነበሩ ነዋሪዎች ርዳታ እየቀረበልን አይደለም አሉ ። የአካባቢው ባለሥልጣናት ርዳታ እየተሰጠ ነው ሲሉ አስተባብለዋል ።...more5minPlay
January 23, 2024የወጣት ሥራ አጥነት እና ሕገ-ወጥ ስደት በትግራይበትግራይ የወጣቶች ሥራ አጥነት እና ሕገ-ወጥ ስደት አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱ ተገለፀ። የኢትዮጵያ ሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር በመጀመርያ ዙር በትግራይ ለሚገኙ 2 ሺህ ወጣቶች የስልጠናና ፋይናንስ ድጋፍ ማድረግ መጀመሩ፥ ከዚህ ውጭም የተለያዩ ፕሮጀክት እየተገበረ እንደሚገኝ አስታውቋል።...more4minPlay
January 23, 2024ሰላም እና የሲቪክ ድርጅቶች አስተዋጽዖኢትዮጵያ ውስጥ ጠባብ የፖለቲካ ምህዳር ቢኖርም ዘላቂ ሰላምን ፣ ተስማምቶ መኖርን እና አብሮነትን ለማጠናከር እና በሰላም ግንባታ ላይ ለመሥራት መቋቋሙን ስርየት ለሁሉም የተባለ ሲቪክ ድርጅት ገለፀ። ሲቪክ ድርጅቱ በማህበረሰብ ውይይት ፣ በትምህርት እና በምርምር ነፃ እና ገለልተኛ ሆኖ ለማገዝ እንደሚንቀሳቀስ ገልጿል።...more3minPlay
January 22, 2024በአማራ ክልል የጥምቀት በዓል እንዴት አለፈ?የጥምቀት በዓል አከባበር በአማራ ክልል ካለው የፀጥታ ሁኔታ አንፃር ችግር ሊፈጠር ይችላል የሚል ሰፊ ስጋት አሳድሮ ነበር፡፡ የክልሉ መንግሥት እንዳለው ግን በዓላቱ ያለምንም የፀጥታ ችግር ተከብረው ተጠናቅቀዋል፡፡ያም ሆኖ በአንዳንድ የምስራቅና ምዕራብ ጎጃም አካባቢዎች በዓሉ በቤተክርስቲያናት አጥር ግቢ ብቻ መከበሩንነዋሪዎቹ አመልክተዋል፡፡...more5minPlay
January 22, 2024ሰሚ ያጣው የደቡብ ዲዛይን ፣ ግንባታና ቁጥጥር ድርጅት ሠራተኞች አቤቱታየሠራተኞቹ ተወካዮች «ድርጅቱ በሠራተኛው ጥረት ትርፋማ በመሆን በርካታ ሀብቶችን አፍርቷል።የሚዘጋውም በኪሳራ ሳይሆን በመንግሥት ትዕዛዝ ነው ፡፡ በመሆኑም በአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ ቁጥር 1156 እና በህብረት ሥምምነት መሠረት ተገቢው ጥቅማ ጥቅሞች እንዲከበሩልን እንፈልጋለን ፡፡ አማራጭ የሥራ ዋስትናችንንም ሊያረጋግጥ ይገባል “ ብለዋል ፡፡...more4minPlay
FAQs about ዜና መጽሔት:How many episodes does ዜና መጽሔት have?The podcast currently has 1,996 episodes available.