*ኢትዮጵያ ከጦር መሣሪያ ሽያጭ ከ30 ሚሊየን ዶላር ያላነሰ ገቢ ማግኘት መቻሏን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ አመለከቱ ።
*ኦነግ እና ኦፌኮ ከሳምንታት በፊት በኦሮሚያ ክልል የጋራ «ሽግግር መንግሥት» እንዲመሠረት ከተለያዩ አካላት አደራ መቀበላቸውን በሚመለከት ያራመዱትን አቋም አራት የፖለቲካ ድርጅቶ ተቃወሙ ።
*ዘ ሔግ በሚገኘው የተመድ ፍርድ ቤት የተባበሩት ዓረብ ኤሚሬቶች የዘር ፍጅት ዓለም አቀፍ ድንጋጌ ተላልፋለች ስትል ሱዳን ክስ መሠረተች ።
*የአውሮጳ ኅብረት መሪዎች «ግልጽ የሆነ አደጋ ተደቅኖባታል» ላሏት አውሮጳ የ800 ቢሊዮን ዩሮ «አውሮጳን ዳግም የማስታጠቅ» እቅድ በጉባኤ ማቅረባቸው ተዘገበ ።