ለአንድ ዓመት ገደማ ከዘለቀ ውጥረት በኋላ ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን ወደነበረበት ለመመለስ እና ለማጠናከር ተስማሙ።
የሱዳን ጦር ወሳኝ እና ስልታዊ ያለውን የዋድ ማዳኒ ከተማን መልሶ መቆጣጠሩን አስታቀወ።
ጀርመን 50 ሚሊዮን ዩሮ ተጨማሪ ድጋፍ ለሶሪያ እንደምትሰጥ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አናሌና ቤርቦክ በሳዑዲ አረቢያ ዋና ከተማ ሪያድ በተሳተፉበት ጉባኤ ላይ ዛሬ ተናገሩ።
በዩናይትድ ስቴትሷ ሎስ አንጀለስ ከተማ እና አካባቢዋ የተከሰተው ሰደድ እሳት የሟቾች ቁጥር ወደ 16 ከፍ ብሏል።
የንጋፋው ፖለቲከኛና የምጣኔ ሐብት ባለሙያ አቶ ቡልቻ ደመቅሳ ስርዓተ ቀብር ዛሬ ተፈፀመ።