በኦሮሚያ ክልል ቄለም ወለጋ ዞን ጅማ ሆሮ ወረዳ ከባድ ዝናብ ባስከተለው የመሬት መናድ የሦስት ሰዎች ሕይወት አለፈ። በንብረት ላይም ከፍተኛ ውድመት ደረሰ።
በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ያለፉት ተማሪዎች ብዛት ከአምናው እንደሚሻል ተገለጸ። እንዲያም ሆኖ ከ1,363 ት/ቤቶች ምንም ተማሪዎች እንዳላለፉ የትምህርት ሚኒስቴር ዛሬ አስታውቋል።
ሰሜን ናይጀሪያ ውስጥ የነዳጅ ቦቴ ሰዎች ካሳፈረ ትልቅ መኪና ጋር ተጋጭቶ በተፈጠረ ፍንዳታ ቢያንስ 52 ሰዎች ሞቱ።
ምዕራባዊ ሶርያ ውስጥ እስራኤል ባደረሰችው የአየር ጥቃት 16 ሰዎች ሲገደሉ፤ በርካቶች መጎዳታቸው ተነገረ። ኢራን ጥቃቱን አውግዛለች።