Sign up to save your podcastsEmail addressPasswordRegisterOrContinue with GoogleAlready have an account? Log in here.
ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና ዜናዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ። የዶይቼ ቬለን ዜናዎች በአፕል ፖድካስት... more
FAQs about የዓለም ዜና:How many episodes does የዓለም ዜና have?The podcast currently has 681 episodes available.
September 05, 2024የነሐሴ 30 ቀን 2016 ዓ.ም. የዓለም ዜናበምዕራብ ጎንደር ዞን መተማ ወረዳ ጋብ ብሎ የነበረው ውጊያ ማገርሸቱን ነዋሪዎች ለዶቼ ቬለ ተናገሩ። ለቀናት ተኩስ እንዳልነበረ የገለጹት እማኞች ዛሬ ከቀትር በኋላ ከ11 ሰዓት ጀምሮ በከተማዋ የተለያየ አካባቢ ተኩስ መከፈቱን አመልክተዋል። ቻይና በቀጣይ ሦስት ዓመታት ለአፍሪቃ ሃገራት ከ50 ቢሊየን ዶላር በላይ የገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ መዘጋጀቷን አስታወቀች።ከሱዳን ተፈናቅለው በኢትዮጵያ ተጠግተው ከነበሩ ስደተኞች 700 የሚሆኑት ወደ ሀገራቸው መመለሳቸው ተነገረ።በጀመርኗ ሙኒክ ከተማ በዛሬው ዕለት ፖሊስ አንድ ተጠርጣሪን ተኩሶ መግደሉ ተነገረ።...more11minPlay
September 03, 2024የነሐሴ 28፣2016 የዓለም ዜና-የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደና ከ-ኤርትራ የሚያደርገዉን በረራ አቋረጠ።የአየር መንገዱ የበላይ ኃላፊ እንዳሉት አየር መንገዳቸዉ በረራዉን ያቋረጠዉ ኤርትራ ባንክ የሚገኝ ገንዘቡ በመታገዱ ነዉ።የዉጪ ዲፕሎማቶች እንደሚሉት ግን አየር መንገዱ በረራዉን ያቋረጠዉ የአዲስ አበባና የአስመራ ግንኙነት ሲበዛ በመሻከሩ ነዉ።----የኢትዮጵያ መንግስት የሰዎችን መታገትና የሚደርስባቸዉን የመብት ጥሰት ለማስቆም ሁነኛ እርምጃ እንዲወስድ የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን በድጋሚ ጠየቀ።-60 ከመቶ የሚሆኑ የአፍሪቃ ወጣቶች ከየሐገራቸዉ መሰደድ እንደሚፈልጉ አንድ ጥናት አረጋገጠ።...more12minPlay
September 02, 2024የነሐሴ 27 ቀን 2016 ዓ.ም የዓለም ዜናየፋኖ ታጣቂዎች ዛሬ የጠረፍ ከተማ የሆነችው መተማ ከተማን ተቆጣጥረው መዋላቸውን የከተማዋ ናዋሪዎች ለዶይቼ ቬሌ ገለጹ።የጀርመን ቀኝ ጽንፈኛ ፓርቲ በሁለት ፌደራል ግዛቶች በተካሄደው ምርጫ ያገኘው ስኬት በመራሄ መንግሥት ኦላፍ ሾልዝ አስተዳደር ላይ ጫና ማስከተሉ እየተነገረ ነው።ሩሲያ በዛሬው ዕለት የተጠናከረ የሚሳኤል ጥቃት በዩክሬን ዋና ከተማ ኪየቭና በሌሎች የሀገሪቱ ከተሞች ላይ ከፈተች።በፓሪስ 2024 ፓራለምፒክ የሚሳተፉ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል እያስመዘገቡ ነው።...more11minPlay
August 31, 2024የነሐሴ 25 ቀን 2016 ዓ.ም የዓለም ዜና*ኢትዮጵያ ፦ በአማራ ክልል ከፍተኛ ዝናብ ያስከተለው ጥፋት*ኬንያ፣ ከፍተኛ የኃይል መቆራረጥ ገጠማት*ቱኒዝያ፣ አደጋ ላይ የነበሩ 28 ስደተኞች ተረፉ*ጀርመን፤ ስድስት ሰዎች በስለት ተወግተው ቆሰሉ*እስራኤል፤ በጄኒን የሚካሄደው ከባድ ውጊያ ቀጥሏል*ኢትዮጵያ ፤ በዓለም ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና 2ኛ ደረጃ ላይ...more9minPlay
August 30, 2024የነሐሴ 24 ቀን 2016 ዓ.ም የዓለም ዜናበማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ማረቆ ልዩ ወረዳ ማንነትን መሠረት ያደረገ ነው በተባለ ጥቃት አራት የአንድ ቤተሰብ አባላትን ጨምሮ ሰባት ሰዎች መገደላቸው ተሰማ። ኢትዮጵያ ሶማሊላንድ ውስጥ ለሚገኘው ቆንስላ ጽሕፈት ቤቷ አዲስ አምባሳደር ሾመች። የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት የኢትዮጵያን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ ከ3,600 በላይ የሕግ ታራሚዎችን በይቅርታ መልቀቁን አስታወቀ። ከታሰሩ የኦነግ አባላት የተለቀቀ የለም። የቀድሞው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ፕሮፌሰር እንድርያስ እሸቴ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ትናንት ሐሙስ ነሐሴ 23 ቀን፣ 2016 ዓ.ም ማረፋቸውን ዩኒቨርስቲው አስታወቀ።...more10minPlay
August 29, 2024የዓለም ዜና፤ ነሐሴ 23 ቀን፤ 2016 ዓ.ም ሐሙስአርስተ ዜና፤ --የአውሮጻ ህብረት የውጭ ጉዳይ ሃላፊ ጆሴፍ ቦሬል በእስራኤል ሚኒስትሮች ላይ ማዕቀብ እንዲጣል ሃሳብ ለማቅረብ እየሰሩ እንደሆነ ተመለከተ። --በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስልጢ ዞን ጎርፍ ከ6ሺህ በላይ ነዋሪዎችን አፈናቀለ። የጎርፍ አደጋው መንሥኤ በአካባቢው ከተገነባ የመስኖ ግድብ ነዉ ተብሏል። በሌላ በኩል በሰሜን ጎንደር ዞን ጠለምት ወረዳ በናዳ ለተጎዱ እርዳታ እየተጠበቀ ነዉ። --ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት «ሂውማን ራይትስ ዋች» በሱዳን ከ16 ወራት በላይ በዘለቀዉ የእርስ በእርስ ግጭት፤ ሁለቱንም ተፋላሚ ወገኖች ፤ የጦርነት ወንጀል ፈፅመዋል ሲል ከሰሰ።...more11minPlay
August 28, 2024የዓለም ዜና፣ ነሐሴ 22፣ 2016-የኢትዮጵያ መንግሥትን በነፍጥ የሚወጉ ኃይላት በሐገሪቱ ብሔራዊ የምክክር ሒደት እንዲካፈሉ ለተደረገላቸዉ ጥሪ መልስ አለመስጠታቸዉን የምክክር ኮሚሽን አስታወቀ።ለታጣቂዎቹ ኃይላት ጥሪዉ የተደረገበትን መንገድና ጥሪዉ ሥለመድረስ አለመድረሱ ግን የኮሚሽኑ ባለሥልጣናት አልጠቀሱም።-----ግብፅ ለሶማሊያ የጦር መሳሪያ ማስታጠቅ ጀመረች።መሳሪያ የጫኑ ሁለት የግብፅ የጦር አዉሮፕላኖች ትናንት ሞቃዲሾ ማረፋቸዉን ዲፕላቶች አስታዉቀዋል።ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋር ወደብ ለመኮናተር ከተስማማች ወዲሕ የሞቃዲሾና የካይሮ ፍቅር ፀጥንቷል...more11minPlay
August 27, 2024የነሐሴ 21 ቀን 2016 ዓ/ም የዓለም ዜናዓርስተ ዜና --የእስራኤል ልዩ ኃይል እጅግ በጣም ውስብስብ ባለው ልዩ ዘመቻ ደቡባዊ ጋዛ ውስጥ ከሚገኝ የሃማስ ዋሻ ውስጥ አንድ ታጋች ማስለቀቁን ዛሬ አስታወቀ። የ52 ዓመቱ ታጋች ከ10 ወራት በፊት ነበር በሃማስ ከደቡባዊ እስራኤል በሃማስ ታጣቂዎች ታግቶ የተወሰደው ።--በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን ሰሞኑን በተከታታይ በደረሰ የመሬት መንሸራተት አደጋ 23 ሰዎች ሞቱ። በአደጋዉ ከሞቱት ሰዎች በተጨማሪ 2700 ያክል ነዋሪዎች ከቤት ንብረታቸዉ ተፈናቅለዋል።--የሱዳን ፈኖ ደራሽ ኃይል በዳርፉር ግዛት በስደተኞች መጠለያ ጣቢያ ላይ በፈጸሙት የከባድ መሳሪያ ጥቃት በትንሹ 20 ሰዎች ተገደሉ።...more11minPlay
FAQs about የዓለም ዜና:How many episodes does የዓለም ዜና have?The podcast currently has 681 episodes available.