የሐምሌ 14 ቀን 2017 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከ40 ሺህ በላይ የመንግሥት ሠራተኞች ያለመደብ መቀጠራቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ በአርባ ምንጭ ከተማ በተካሄደው የክልሉ 6ኛ ዙር 5ኛ መደበኛ ጉባኤ ላይ ተናገሩ።
የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዶሚር ዜሌንስኪ፣ በኬቭ እና በሞስኮ መካከል የሚካሄደው ጦርነት እንዲቆም ባቀረቡት 3ተኛ ዙር የድርድር ሀሳብ እንደምትስማማ ክሬምሊን ዛሬ አረጋገጠች።
የእስራኤል ጦር ወደ ጋዛው ዴር አልባላህ ዛሬ ታንኮቹን አሰማራ። ጦሩ ታንኮቹን ያሰማራባት ዴር አልባላህ የተቀሩት የእስራኤል ታጋቾች ይገኙበታል ብሎ በሚያምነበት የሚያምንበት አካባቢ ነው።