Sign up to save your podcastsEmail addressPasswordRegisterOrContinue with GoogleAlready have an account? Log in here.
ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና ዜናዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ። የዶይቼ ቬለን ዜናዎች በአፕል ፖድካስት... more
FAQs about የዓለም ዜና:How many episodes does የዓለም ዜና have?The podcast currently has 680 episodes available.
December 21, 2024የታህሳስ 12 ቀን 2017 የዓለም ዜናየኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) የፋኖ ኃይሎች በኦሮሚያ ክልል ወለጋ አከባቢ ዕዝ እንዲመሰርቱ መንግስት ድጋፍ አድርጓል ሲል ከሰሰ፡፡በጀርመን በደረሰው ጥቃት 5ሞቱ ከ200 በላይ ቆሰሉ...more11minPlay
December 19, 2024የሐሙስ ታኅሣሥ 10 ቀን፣ 2017 ዓ.ም የዓለም ዜና*ባለፈው ሰኞ በመቅረዝ ጠቅላላ ሆስፒታል የቅድመ ካንሰር ምርመራ የተደረገላቸውና በእሥር ላይ ያሉት አቶ ክርስትያን ታደለ እና አቶ ዮሐንስ ቧያለው ዛሬም ሆስፒታል ሳይወሰዱ መቅረታቸው ተነገረ ። *በዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል የሚመራው ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ቡድን «አዲስ» ያለውን የትግል አቅጣጫ እንደሚከተል ዐሳወቀ ።*በውጭ አገራት የርዳታ ተግባር ላይ ተሰማርተው የነበሩ ከ280 በላይ ሠራተኞች ባለፉት 12 ወራት ውስጥ ብቻ መገደላቸው ተገለጠ ።*ጀርመን ውስጥ ከማኅበረሰቡ ጋር ያልተዋሐዱ ሶሪያውያን ሊባረሩ ይገባል ሲሉ አንድ ከፍተኛ ፖለቲከኛ ተናገሩ ።...more10minPlay
December 18, 2024የታኅሳስ 9 ቀን 2017 ዓ.ም. የዓለም ዜናየታኅሳስ 9 ቀን 2017 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና የኢትዮጵያ መንግሥት የመብቶች እና ዴሞክራሲ ማዕከል የተባለውን የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅት ዳግም «ከማንኛውም የሥራ እንቅስቃሴ» አገደ። የአውሮጳ ኅብረት በሶሪያ ላይ የጣላቸውን አንዳንድ የኤኮኖሚ ማዕቀቦች ማንሳትን እንደገና ሊያጤን እንደሚችል አስታወቀ። የፈረንሳይ ከፍተኛ ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት የቀድሞው ፕሬዝዳንት ኒኮላ ሳርኮዚ በሙስና እና ስልጣናቸውን አለአግባብ በመጠቀም ተከሰው የተበየነባቸውን ውሳኔ አፀና። ፍርድ ቤቱ ሳርኮዚ እንቅስቃሴያቸውን የሚከታተል የኤሌክትሮኒክ መሳሪያ ለአንድ ዓመት እንዲያደርጉም አዟል።...more11minPlay
December 17, 2024የማክሰኞ ታኅሣሥ 8 ቀን፣ 2017 ዓ.ም የዓለም ዜናበአማራ ክልል ጎጃም ቀጣና በፋኖ ትዕዛዝ ለሳምንት ተዘግቶ የቆየው የእንቅስቃሴ ገደብ ከዛሬ ጠዋት ጀምሮ አገልግሎት መስጠት መጀመሩ ተገለጠ ። መንገዶቹ መከፈታቸውን አንዳንድ ተገልጋዮች ለዶይቸ ቬለ ተናግረዋል ።የውጭ ባንኮች ኢትዮጵያ ውስጥ ገብተው እንዲሠሩ የሚፈቅድ አዋጅ ዛሬ ጸደቀ ። አዋጁ በሦስት ተቃውሞ፤ በአብላጫ ድምፅ መጽደቁ ተገልጧል ። ሩስያ ከፍተኛ የጦር መኮንኗን ሞስኮ ውስጥ በተጠመደ ቦንብ ፍንዳታ አጣች ። የ54 ዓመቱ ሩስያዊ ሊውቴናንት ጄኔራል ከረዳታቸው ጋር ዛሬ ጠዋት የተገደሉት በእግር ተረግጦ በሚገፋ የኤሌክትሪክ መጓጓዣ ወይንም ስኩተር ላይ በተጠመደ ፈንጂ ፍንዳታ መሆኑ ተዘግቧል ።...more11minPlay
December 16, 2024የዓለም ዜና፤ ታህሳስ 7 ቀን 2017 ዓ.ም ሰኞ--ባለፉት 8 ቀናት በጎጃም ቀጠና የነበረው የእንቅስቃሴ ገደብ መነሳቱን የአማራ ፋኖ በጎጃም አስታወቀ። የአማራ ፋኖ በጎጃም የህዝብ ግንኙነት መምሪያ ምክትል ኃላፊ እንደሆኑ የገለፁልን ዮሐንስ ዓለማየሁ ባለፉት 8 ቀናት በጎጃም ቀጠና አንዳንድ አካባቢዎች በተደርጉ ውጊያዎች ህብረተሰቡ በመንግድ ሊገጥመው የሚችለውን ሞትና እንግልት ለማስወገድ የመንገድና የንግድ እንቅስቃሴዎች ላይ ገደብ ተጥሎ መቆየቱን ተናግረዋል።-- የቱርኩ ፕሬዚዳንት ራቺብ ታይብ ኤርዶጋን በቅርቡ ኢትዮጵያን እና ሶማልያን እንደሚጎበኙ ተነገረ።--የሶርያዉ ባሽር አልአሳድ ከሶሪያ አቅጄ አልወጣሁም ለመዉጣትም እቅድ አልነበረኝም፤ የወጣሁት በሩስያ ነዉ አሉ።...more13minPlay
December 15, 2024የታህሳስ 6 ቀን 2017 የዓለም ዜናበሱዳን በድሮን ጥቃት 3 ስቪሎች መገደላቸውንና ከ20 በላይ መቁሰላቸውንያለውጤት የተበተነው ድርድር ቱርክ የበሽር አልአሳድን መንግስት ለገረሰሱት አማጽያን ወታደራዊ ድጋፍ ለመስጠት ዝግጁ እንደሆነችከ7,500 የሚበልጡ ሶሪያውያን ስደተኞች ከቱርክ ወደሐገራቸው መግባታቸውን...more10minPlay
December 14, 2024የታኅሳስ 5 ቀን 2017 ዓ.ም. የዓለም ዜናኢትዮጵያዊ ባለሀብት በደቡብ ሱዳን ታጣቂዎች ጋምቤላ ክልል ተገደሉ፤ የCOP16 ጉባኤ ያለ አርኪ ውጤት ተጠናቀቀ፤የጀርመኑ ፕሬዚዳንት የአራት ቀናት የአፍሪቃ ጉዟቸውን አጠናቀቁ፤የጀርመን መራኄ መንግሥት ኦላፍ ሾልስ ፓርቲያቸው በዋና እጩነት መረጣቸው፤የድንበር የለሽ የሀኪሞች ቡድን መርከብ ስራ ለማቆም ተገደደች፤የደቡብ ኮሪያው ፕሬዝዳንት ዩን ከስልጣን እንዲወርዱ የሀገሪቱ ምክር ቤት ወሰነ...more11minPlay
December 13, 2024የአርብ ታኅሳስ 4 ቀን 2017 ዓ.ም. የዓለም ዜናየአርብ ታኅሳስ 4 ቀን 2017 ዓ.ም. አርዕስተ ዜናኢትዮጵያ እና ሶማሊያ በመካከላቸው የተፈጠረውን ውዝግብ ለመፍታት «ቴክኒካዊ ውይይት» ለማድረግ መስማማታቸውን የአፍሪቃ ኅብረት ፣ኢጋድ ፣ዩናይትድ ስቴትስና የተመድ አወደሱ ። አምነስቲ ኢንተርናሽናል የሱዳን ጦር ሕዝብ በብዛት በተሰበሰበበት የገበያ ስፍራ የፈጸመው የአየር ጥቃት ግልፅ የጦር ወንጀል ነው አለ። ተመራጩ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ዩክሬን ዩናይትድ ስቴትስ በሰጠቻት የጦር መሣሪያዎች በሩስያ ምድር የሚገኙ ዒላማዎችን እንድትመታ እንደማይፈቅዱ ተናገሩ።...more10minPlay
FAQs about የዓለም ዜና:How many episodes does የዓለም ዜና have?The podcast currently has 680 episodes available.