የኅዳር 26 ቀን 2017 ዓም አርዕስተ ዜና
በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ላስታ ወረዳ “ ብልባላ” በተባለች መንደር ባለፈው ማክሰኞ ሌሊት ተፈፀመ በተባለ የድሮን ጥቃት አንዲት የ83 ዓመት እናታቸው እንደተገደሉባችው የሟች ልጅ ለዶቼቬለ ተናገሩ።
የቀድሞ የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ታዬ ደንደዓ፤ ዛሬ ህዳር 26 ቀን 2017 ዓ.ም. እኩለ ቀን ላይ ከእስር ተለቀው ቤታቸው መግባታቸውን ባለቤታቸው ወ/ሮ ስንታየሁ ዓለማየሁ ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል፡፡
የፈረንሳይ ጠ/ሚ ሚሼል ባርንየ የስራ መልቀቂያ ቢያስገቡም የማክሮ ጽህፈት ቤት እንዳለው ባርንየ አዲስ መንግሥት እስኪሰየም ድረስ ከሚኒስትሮቻቸው ጋር በሞግዚትነት ይቆያሉ ።