Sign up to save your podcastsEmail addressPasswordRegisterOrContinue with GoogleAlready have an account? Log in here.
FAQs about DW | Amharic - News:How many episodes does DW | Amharic - News have?The podcast currently has 732 episodes available.
August 12, 2025በኢትዮጵያ መፍትሔ ያላገኘው እገታከሳምንት በፊት ከአዲስ አበባ ወደ ደብረማርቆስ መንገደኞችን አስፍሮ ይጓዝ ከነበረ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ከ20 በላይ ተሳፋሪዎች ታግተው መወሰዳቸውን ከእገታው ያመለጠ ተሳፋሪ አመለከተ።...more4minPlay
August 12, 2025ጀርመን ፣ እስራኤል ለጋዛ ጦርነት የሚውሉ የጦር መሣሪያዎችን ማቅረብ ለማቆም መወሰኗጀርመን ለጋዛ ጦርነት የሚውሉ የጦር መሣሪያዎችን ለእስራኤል ማቅረብ እንደምታቆም ማሳወቋ ሰሞኑን ትኩረት ከሳቡት ጉዳዮች መካከል አንዱ ነው። የጀርመን መንግሥት እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰው የእስራኤል የፀጥታ ካቢኔ ጋዛ ሲቲን ለመቆጣጠር ያለመ ወታደራዊ ዘመቻ ለማካሄድ ባለፈው ሳምንት ከተስማማ በኋላ ነው። እሥራኤል የጀርመንን ውሳኔ ተቃውማለች...more11minPlay
August 12, 2025ሕገ ወጥ የወርቅ ማዕድን ቁፋሮ በትግራይበባህላዊ እና ዘመናዊ መንገድ የሚደረገው የወርቅ ማውጣት ስራ ለበርካታ ዜጎች የገቢ ምንጭ ሆኖ እንዳለ የሚነገር ሲሆን ከዚህ በተቃራኒ ደግሞ ሕገወጥ የወርቅ እና ሌሎች ማዕድናት በትግራይ መንሰራፋታቸው ተከትሎ የአካባቢ ተፈጥሮ ሀብት ውድመት እና ብክለት በስፋት እየተስተዋለ ስለመሆኑም ተገልጿል።...more4minPlay
August 12, 2025ዉጫሌና አካባቢዉ የሠፈሩ ተፈናቃዮች ለረሐብ ተጋልጠናል አሉበውጫሌ እና አካባቢው ያሉ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችየመጠለያ ጣቢያ የሌላቸው እና ከማህበረሰቡ ጋር ተቀላቅለውእንዲኖሩ የተደረጉ ቢሆንም አሁን የምግብ እጥረቱ ከፍተኛበመሆኑ እናቶች ልጆቻቸውን ትተው እየሞቱ ነው ይላሉተፈናቃዮቹ፡...more4minPlay
August 12, 2025የቆዳ በሽታ ከሆኑት አንዱ ስለሆነው ቡግንጅ ምን ያውቃሉ?ብጉንጅ በርካቶችን ከሚያጠቁ የቆዳ በሽታዎች አንዱ መሆኑን የህክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። አንዳንዶች ቡግንጅን በተለምዶ የደም መቆሸሽ እየተባለ በሚነገር ምክንያት የሚከሰት አድርገው ይገልጹታል። ምን ያገናኘዋል?...more11minPlay
August 12, 2025ኢሰመኮ፣ የሲቪክ ማኅበረሰብ ድርጅቶች ረቂቅ እንዲሻሻል ያደረገዉ ግፊት ውጤት ማምጣቱን አስታወቀረቂቅ ማሻውያ የውጭ ድርጅቶች እና ኢትዮጵያ ውስጥ በሚኖሩ የውጭ ሀገር ዜጎች የተመሰረቱ ሀገር በቀል [ሲቪክ] ድርጅቶች የፖለቲካ ፓርቲዎችን በማግባባትም ሆነ ግፊት በማድረግ ተፅዕኖ መፍጠር፣ በመራጮች ትምህርት ወይም በምርጫ መታዘብ ሥራ ላይ መሠማራት አይችሉም" የሚል ሀሳብም ይዟል።...more3minPlay
August 11, 2025የመንገዶች መዘጋትና መከፈት በጎጃም ቀጠናየምዕራብ ጎጃም ዞን ደንበጫ ከተማ ነዋሪ ባለፈው አርብ በእጀብ ሲጓዙ የተወሰኑ መኪናዎችን ሲያልፉ ማየታቸውን ተናግረዋል።በከተማው ውስጥ የባጃጆች እንቅስቃሴ እንደነበር ጠቁመው፣ ከዚያ ውጪ ወደየትኛውም አቅጣጫ የሚጓዝ የህዝብ ትራንስፖርት እንዳልነበረ ተናግረዋል፡፡የአማራ ፋኖ በጎጃም ባሰራጨው አዲስ መረጃ፣ እገዳው ላይ ማሻሻያ ማድረጉን አመልክቷል፣...more4minPlay
August 11, 2025የብልፅግና ፓርቲ መግለጫ፤ የሌሎች ፓርቲዎች አስተያየትሰላማዊ የፖለቲካ ዕድሎችን" አሟጥጦ እንደሚጠቀም የገለፀው ብልጽግና ፓርቲ "ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ለውጦች አንሠራርተዋል" ሲል ደምድሟል። ለኦፌኮ ይህ አልተዋጠለትም።«በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ለሚወስኑ ታጣቂዎች አስፈላጊውን ሁሉ ለማድረግ ሕግ ለማስከበር»መዘጋጀቱን ፓርቲው አስታውቋል። የኢሶዴፓ ሊቀመንበር ዶክተር ራሔል ባፌ ግን ይህን ይጠራጠራሉ።...more4minPlay
August 11, 2025ከሕጋዊ የዋጋ ተመን በላይ የሚሸጠው ነዳጅ ያስከተለው ፈተናከማደያ ውጪ የነዳጅ ችርቻሮ ላይ ከ200 በር በላቀ ዋጋ ነዳጅ እንደሚሸጥ የገለጹት ተጠቃሚው፤ “አሁን ባለፈው ሳምንት አማራጭ ሳጣ አዋሽ ለማን አከባቢ ለመኪና አንድ ጄሪካን ነዳጅ በ7000 ብር ማለትም አንዷን ሊትር ከ200ብር በላይ ሂሳብ ሞልቼ አልፌያለሁ” ፖሊስ እና የንግድ ቁጥጥር ሰራተኞች በቆሙበትም ነዳጅ በ140 ስሸጥ ይታያል” ብለዋል።...more4minPlay
August 11, 2025በትግራይ ክልል ኃይሎችና በቀድሞ አባላቱ መካከል የተካሄደ ግጭትበተጋሩ መካከል የእርስ በርስ ግጭት እንዳይከሰት ጥረት እያደረገ እንዳለ የሚገልፀው የትግራይ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ፥ በስም ያልጠራቸው ይሁንና 'ወዶገብ፣ ነጭ ለባሽ' በሚሉ እና ሌሎች አገላለፃች ያስቀመጣቸው አካላት ተጋሩን እርስበርስ ለማዋጋት ፕሮጀክት በመያዝ አፋር ያሉ ታጣቂዎችን ተጠቅመው በትግራይ ኃይሎች ላይ ጥቃት ሰንዝረዋል ብሏል።...more3minPlay
FAQs about DW | Amharic - News:How many episodes does DW | Amharic - News have?The podcast currently has 732 episodes available.