ጋምቤላ ክልል በ4 ወረዳዎች የተከሰተ «ኮሌራ መሰል» በሽታ የዘጠኝ ሰዎችን ሕይወት ቀጠፈ።
በሶማሊያዋ ፑንትላንድ ከ240 በላይ እራሴን «እስላማዊ መንግሥት» የሚለው ታጣቂ ቡድን አባላት መገደላቸው ተገለጸ።
የሩሲያው ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን ከፍተኛ ዲፕሎማትና የክሬምሊን አማካሪያቸውን ወደ ሳውድ አረቢያ ላኩ። የዩክሬንን ጦርነት ለማስቆም ለሚካሄደው ውይይት አዲሱ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሮቢዮ ሳውዲ ገብተዋል።
የዩክሬን ፕሬዝደንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ ኪየቭን ያላካተተ ውይይት ውጤት አይኖረውም አሉ።
የእስራኤል ጦር ዛሬ ደቡባዊ ሊባኖስ ውስጥ ባካሄደው የአየር ድብደባ የሀማስን የጦር አዛዥ መግደሉን አስታወቀ።